የሀላባ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 10ኛ ዓመት የስራ ዘመን 19ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው
ሀዋሳ፣ ነሐሴ 10/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሀላባ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 10ኛ ዓመት የስራ ዘመን 19ኛ መደበኛ ጉባኤውን በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡
በዞኑ ዋና አፈጉባኤ አቶ መሀመድአሚን ሀጂ ማሕዲ በመክፈቻ ንግግራቸው እንዳሉት በስራ ዘመኑ በየደረጃው የሚገኙ የምክር ቤት አባላት በዞኑ በተለያዩ አካባቢዎች እየተሰሩ የሚገኙ ልማቶችን በመከታተል እና ግብር መልስ መስጠት በመቻሉ የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ ተችሏል፡፡
በግብርና ግብዓት አጠቃቀም እና አመላለስ ተግባር በርካታ ስራዎችም ተሰርተው ውጤትመመዝገቡን የገለጹት አፈ ጉባኤው የዞኑን ውስን የመንግስት ሀብት በመጠቀም የተለያዩ የልማት ስራዎችን ለማልማት የግብር አሰባሰብ ተግባር ስራ በተጠናከረ መልኩ መሠራቱን ጠቅሰዋል።
በከተማ ደረጃም የቁሊቶን ከተማ ውብት ለማስጠበቅ የኮሪዳር ልማት ስራ እየተሰራ ስለመሆኑ ገልጸዋል።
የሀላባ ዞን የቁሊቶ ከተማ አለም አቀፍ የስተዲየም ግንባታ በህብረተሰቡ ተሳትፎ ትኩራት ተሰጥቶበት እየተሰራ በመሆኑ እና በሀገር እና ከሀገር ውጪ ገቢ የማሰባሰብ ተግብር ተጠናክሮ መቀጠሉን ነው አቶ መሀመድአሚን ሀጂ መሐዲ የገለጹት።
በጉኤው የ2017 በጀት አመት አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2018 በጀት አመት ጠቋሚ እቅድና ረቂቅ በጀት ቀርቦ ይጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ዘጋቢ፡- አብድልሀፊዝ መሐመድ
More Stories
የሀድያ የልማት እድገት፣ አንድነትና የመተባበር መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማረቆ ልዩ ወረዳ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ተኛ ዙር 12ተኛ ዓመት 5ተኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው
ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀድያ ዞን በ4 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር እየተገነባ ያለው የእህል ማከማቻ ዲፖ ጎበኙ