የሀላባ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 10ኛ ዓመት የስራ ዘመን 19ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው
ሀዋሳ፣ ነሐሴ 10/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሀላባ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 10ኛ ዓመት የስራ ዘመን 19ኛ መደበኛ ጉባኤውን በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡
በዞኑ ዋና አፈጉባኤ አቶ መሀመድአሚን ሀጂ ማሕዲ በመክፈቻ ንግግራቸው እንዳሉት በስራ ዘመኑ በየደረጃው የሚገኙ የምክር ቤት አባላት በዞኑ በተለያዩ አካባቢዎች እየተሰሩ የሚገኙ ልማቶችን በመከታተል እና ግብር መልስ መስጠት በመቻሉ የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ ተችሏል፡፡
በግብርና ግብዓት አጠቃቀም እና አመላለስ ተግባር በርካታ ስራዎችም ተሰርተው ውጤትመመዝገቡን የገለጹት አፈ ጉባኤው የዞኑን ውስን የመንግስት ሀብት በመጠቀም የተለያዩ የልማት ስራዎችን ለማልማት የግብር አሰባሰብ ተግባር ስራ በተጠናከረ መልኩ መሠራቱን ጠቅሰዋል።
በከተማ ደረጃም የቁሊቶን ከተማ ውብት ለማስጠበቅ የኮሪዳር ልማት ስራ እየተሰራ ስለመሆኑ ገልጸዋል።
የሀላባ ዞን የቁሊቶ ከተማ አለም አቀፍ የስተዲየም ግንባታ በህብረተሰቡ ተሳትፎ ትኩራት ተሰጥቶበት እየተሰራ በመሆኑ እና በሀገር እና ከሀገር ውጪ ገቢ የማሰባሰብ ተግብር ተጠናክሮ መቀጠሉን ነው አቶ መሀመድአሚን ሀጂ መሐዲ የገለጹት።
በጉኤው የ2017 በጀት አመት አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2018 በጀት አመት ጠቋሚ እቅድና ረቂቅ በጀት ቀርቦ ይጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ዘጋቢ፡- አብድልሀፊዝ መሐመድ

More Stories
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ
የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ለአካባቢው ማህበረሰብ ለውጥ የሚበጅ፤ ዘመኑን በሚዋጅ የቴክኖሎጂ እውቀት የበለጸጉ ዜጎች የሚፈልቁበት ተቋም ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ