የሀላባ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 10ኛ ዓመት የስራ ዘመን 19ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው
ሀዋሳ፣ ነሐሴ 10/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሀላባ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 10ኛ ዓመት የስራ ዘመን 19ኛ መደበኛ ጉባኤውን በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡
በዞኑ ዋና አፈጉባኤ አቶ መሀመድአሚን ሀጂ ማሕዲ በመክፈቻ ንግግራቸው እንዳሉት በስራ ዘመኑ በየደረጃው የሚገኙ የምክር ቤት አባላት በዞኑ በተለያዩ አካባቢዎች እየተሰሩ የሚገኙ ልማቶችን በመከታተል እና ግብር መልስ መስጠት በመቻሉ የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ ተችሏል፡፡
በግብርና ግብዓት አጠቃቀም እና አመላለስ ተግባር በርካታ ስራዎችም ተሰርተው ውጤትመመዝገቡን የገለጹት አፈ ጉባኤው የዞኑን ውስን የመንግስት ሀብት በመጠቀም የተለያዩ የልማት ስራዎችን ለማልማት የግብር አሰባሰብ ተግባር ስራ በተጠናከረ መልኩ መሠራቱን ጠቅሰዋል።
በከተማ ደረጃም የቁሊቶን ከተማ ውብት ለማስጠበቅ የኮሪዳር ልማት ስራ እየተሰራ ስለመሆኑ ገልጸዋል።
የሀላባ ዞን የቁሊቶ ከተማ አለም አቀፍ የስተዲየም ግንባታ በህብረተሰቡ ተሳትፎ ትኩራት ተሰጥቶበት እየተሰራ በመሆኑ እና በሀገር እና ከሀገር ውጪ ገቢ የማሰባሰብ ተግብር ተጠናክሮ መቀጠሉን ነው አቶ መሀመድአሚን ሀጂ መሐዲ የገለጹት።
በጉኤው የ2017 በጀት አመት አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2018 በጀት አመት ጠቋሚ እቅድና ረቂቅ በጀት ቀርቦ ይጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ዘጋቢ፡- አብድልሀፊዝ መሐመድ
More Stories
ግራሃም ፖተር የሲዊዲን ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ በመሆን ተሾሙ
የፌደሬሽን ምክር ቤት እና ተጠሪ ተቋማት በካፋ ዞን ሺሺንዳ ከተማ አስተዳደር ለአቅመ-ደካሞች ያስገነቧቸውን መኖሪያ ቤቶች እያስረከቡ ነው
የወባ በሽታ ስርጭትን በዘላቂነት መቀነስ እንዲቻል በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ