በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማረቆ ልዩ ወረዳ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ተኛ ዙር 12ተኛ ዓመት 5ተኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው
ሐዋሳ፣ ነሐሴ10/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ምክር ቤቱ 4ተኛ ዙር 12ተኛ ዓመት 5ተኛ መደበኛ ጉባኤው በቆሼ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል።
የማረቆ ልዩ ወረዳ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ሻምበል ደበሮ ልዩ ወረዳው የሰላምና የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ እየተሰራ ስለመሆኑ ጠቁመዋል።
የልዩ ወረዳው ህዝብ በሁሉም ዘርፎች ተጠቃሚነታቸው እንዲረጋገጥ እየሰራን ነው ብለዋል።
በጉባኤው የልዩ ወረዳው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጉባኤ አጀንዳዎችን መርምሮ ማጽደቅ ፣ የአስተዳደር ጽ/ቤት፣የምክር ቤት፣የከፍተኛ ፍ/ቤት አፈጻጸሞችን ሪፖርት እና የ2018 ረቂቅ በጀትን መርምሮ ማጽደቅ የጉባኤው መርሀ ግብሮች ናቸው።
የማረቆ ልዩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጀማል አማሮ የ2017 በጀት ዓመት የአፈጻጸም ሪፖርት ለምክር ቤት አባላቱ በማቅረብ ላይ ናቸው።
ዘጋቢ :- አብደላ በድሩ

More Stories
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ
የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ለአካባቢው ማህበረሰብ ለውጥ የሚበጅ፤ ዘመኑን በሚዋጅ የቴክኖሎጂ እውቀት የበለጸጉ ዜጎች የሚፈልቁበት ተቋም ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ
የሴቶችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ለውጥ የሚገድቡ እንቅፋቶችን በትብብር መፍታት እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ዘቢባ መሀመድናስር ገለጹ