በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማረቆ ልዩ ወረዳ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ተኛ ዙር 12ተኛ ዓመት 5ተኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው
ሐዋሳ፣ ነሐሴ10/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ምክር ቤቱ 4ተኛ ዙር 12ተኛ ዓመት 5ተኛ መደበኛ ጉባኤው በቆሼ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል።
የማረቆ ልዩ ወረዳ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ሻምበል ደበሮ ልዩ ወረዳው የሰላምና የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ እየተሰራ ስለመሆኑ ጠቁመዋል።
የልዩ ወረዳው ህዝብ በሁሉም ዘርፎች ተጠቃሚነታቸው እንዲረጋገጥ እየሰራን ነው ብለዋል።
በጉባኤው የልዩ ወረዳው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጉባኤ አጀንዳዎችን መርምሮ ማጽደቅ ፣ የአስተዳደር ጽ/ቤት፣የምክር ቤት፣የከፍተኛ ፍ/ቤት አፈጻጸሞችን ሪፖርት እና የ2018 ረቂቅ በጀትን መርምሮ ማጽደቅ የጉባኤው መርሀ ግብሮች ናቸው።
የማረቆ ልዩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጀማል አማሮ የ2017 በጀት ዓመት የአፈጻጸም ሪፖርት ለምክር ቤት አባላቱ በማቅረብ ላይ ናቸው።
ዘጋቢ :- አብደላ በድሩ
More Stories
ግራሃም ፖተር የሲዊዲን ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ በመሆን ተሾሙ
የፌደሬሽን ምክር ቤት እና ተጠሪ ተቋማት በካፋ ዞን ሺሺንዳ ከተማ አስተዳደር ለአቅመ-ደካሞች ያስገነቧቸውን መኖሪያ ቤቶች እያስረከቡ ነው
የወባ በሽታ ስርጭትን በዘላቂነት መቀነስ እንዲቻል በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ