በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማረቆ ልዩ ወረዳ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ተኛ ዙር 12ተኛ ዓመት 5ተኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው
ሐዋሳ፣ ነሐሴ10/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ምክር ቤቱ 4ተኛ ዙር 12ተኛ ዓመት 5ተኛ መደበኛ ጉባኤው በቆሼ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል።
የማረቆ ልዩ ወረዳ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ሻምበል ደበሮ ልዩ ወረዳው የሰላምና የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ እየተሰራ ስለመሆኑ ጠቁመዋል።
የልዩ ወረዳው ህዝብ በሁሉም ዘርፎች ተጠቃሚነታቸው እንዲረጋገጥ እየሰራን ነው ብለዋል።
በጉባኤው የልዩ ወረዳው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጉባኤ አጀንዳዎችን መርምሮ ማጽደቅ ፣ የአስተዳደር ጽ/ቤት፣የምክር ቤት፣የከፍተኛ ፍ/ቤት አፈጻጸሞችን ሪፖርት እና የ2018 ረቂቅ በጀትን መርምሮ ማጽደቅ የጉባኤው መርሀ ግብሮች ናቸው።
የማረቆ ልዩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጀማል አማሮ የ2017 በጀት ዓመት የአፈጻጸም ሪፖርት ለምክር ቤት አባላቱ በማቅረብ ላይ ናቸው።
ዘጋቢ :- አብደላ በድሩ

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ