የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2018 የትምህርት ዘመን የዝግጅት ምዕራፍ ስራዎች እና የ3ኛው ዙር “ትምህርት ለትውልድ” ማስጀመሪያ መድረክ በወራቤ ከተማ እየተካሄደ ነው

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2018 የትምህርት ዘመን የዝግጅት ምዕራፍ ስራዎች እና የ3ኛው ዙር “ትምህርት ለትውልድ” ማስጀመሪያ መድረክ በወራቤ ከተማ እየተካሄደ ነው

የማስጀመሪያ መድረኩ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ በተገኙበት ነው እየተካሄደ የሚገኘው።

በዚሁ ማስጀመሪያ መድረክ ላይ የ2017 የትምህርት ዘመን የክረምት ወራት ስራዎች እና የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማትና ግብዓት ለማሟላት የተዘጋጀ “የትምህርት ለትውልድ” የንቅናቄ ዕቅድ ይቀርባል።

በተጨማሪም የትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራም አተገባበር፣ የተመዘገቡ ውጤቶችና ቀጣይ አቅጣጫዎች እንዲሁም በሴቭ ዘ ችልድረን የተከናወኑ ተግባራት አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ይደረግበታል ተብሏል።

በመድረኩ ከክልል እስከ ወረዳ የሚገኙ ባለድርሻ አካላት መገኘታቸውን የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ያወጣው መረጃ ያመላክታል፡፡