የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2018 የትምህርት ዘመን የዝግጅት ምዕራፍ ስራዎች እና የ3ኛው ዙር “ትምህርት ለትውልድ” ማስጀመሪያ መድረክ በወራቤ ከተማ እየተካሄደ ነው
የማስጀመሪያ መድረኩ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ በተገኙበት ነው እየተካሄደ የሚገኘው።
በዚሁ ማስጀመሪያ መድረክ ላይ የ2017 የትምህርት ዘመን የክረምት ወራት ስራዎች እና የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማትና ግብዓት ለማሟላት የተዘጋጀ “የትምህርት ለትውልድ” የንቅናቄ ዕቅድ ይቀርባል።
በተጨማሪም የትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራም አተገባበር፣ የተመዘገቡ ውጤቶችና ቀጣይ አቅጣጫዎች እንዲሁም በሴቭ ዘ ችልድረን የተከናወኑ ተግባራት አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ይደረግበታል ተብሏል።
በመድረኩ ከክልል እስከ ወረዳ የሚገኙ ባለድርሻ አካላት መገኘታቸውን የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ያወጣው መረጃ ያመላክታል፡፡

More Stories
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል
በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ የምግብ ዋስትና ፕሮጀክት እየተስተዋለ ያለውን ድህነት እና የስራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ ያበረከተው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑ ተገለጸ