ከ1 መቶ ሺህ በላይ መራጮች የ2017 የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምርጫ እንደሚሳተፉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ገለጸ
ምርጫው ከነሃሴ 9 እስከ 11/2017 ዓ. ም እንደሚካሄድም ምክር ቤቱ አስታውቋል፡፡
የክልሉ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የ2017 ዓ. ም ምርጫ አስፈፃሚ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ጀማል አባመጫ በጉዳዩ ላይ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
ከፌደራል ጀምሮ የሚደረገው የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት መጅሊስ ማቋቋሚያ ምርጫ የረጂም ጊዜ የህዝበ ሙስሊሙ ጥያቄ እንደነበር አቶ ጀማል በመግለጫቸው አንስተዋል፡፡
በክልሉ ሁሉም ዞኖች ምርጫው ይካሄዳል ያሉት አቶ ጀማል ነገር ግን በአንዳንድ ችግሮች ምክንያት ምርጫ የማይካሄድባቸው መስኪዶች እንዳሉም ጠቅሰዋል፡፡
በዚህም የድምጽ መስጫ ቀኑ ከነሃሴ 9 ጀምሮ እስከ ነሃሴ 11 ቀን 2017 ዓመተ ምህረት እንደሚካሄድ አስታውቀዋል፡፡
ምርጫው በአምስት ዘርፎች ማለትም በኡለማዎች፣ በምሁራን፣ በወጣቶች፣ በሴቶችና በሥራ ማህበራት ዘርፎች እንደሚካሄድ ነው አቶ ጀማል የገለጹት፡፡
በምርጫው 1 መቶ 5 ሺህ 1 መቶ 61 መራጮች በክልል ደረጃ መመዝገባቸውን አስታውቀዋል፡፡
ምርጫው ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊ፣ አካታችና ፍትሃዊ በሆነ መልኩ እንዲካሄድ በሁሉም መስኪዶች ውይይት መደረጉንም ነው የተናገሩት፡፡
ከክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ጋርም በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ዘጋቢ፡- ዳንኤል መኩሪያ

More Stories
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል
በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ የምግብ ዋስትና ፕሮጀክት እየተስተዋለ ያለውን ድህነት እና የስራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ ያበረከተው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑ ተገለጸ