የሴቶችን ተሳትፎ ማሳደግና አካታች በሆኑ እቅዶች መመራት እንደሚገባ ተገለጸ
ሀዋሳ፡ ነሐሴ 07/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሴቶችን ተሳትፎ ማሳደግና አካታች በሆኑ እቅዶች መመራት እንደሚገባ በካፋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ረዳት የመንግስት ተጠሪና የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወይዘሮ ጽዮን ታዬ ገለጹ።
ኃላፊዋ ይህንን የገለጹት የፓርቲውን የ2018 በጀት ዓመት የተግባር ዕቅድ ባቀረቡበት መድረክ ነው።
በአመራሮችና በአባላቱ ዘንድ የብልጽግናን እሳቤ በማስረጽና የአቅም ግንባታ ስራዎች ላይ በማተኮር የፓርቲውን አደረጃጀት ለማሳደግ ይሰራል ብለዋል።
ሀገር-አቀፍና ዓለም-አቀፍ ነባራዊ ሁኔታዎችን በመገንዘብና በእውቀት ላይ የተመሠረተ የአሰራር ስርዓትን በመዘርጋት ተግባራትን መከወን አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።
በፓርቲው ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ የተቀመጡ የውሳኔ አቅጣጫዎችን መነሻ በማድረግ የመልካም አስተዳደር ስራዎች በህዝብ ተሳትፎ እንዲጎለብቱ ይሰራል ብለዋል።
የሴቶችን ተሳትፎ በማሳደግ አካታች፣ አሳታፊ እና ሁሉን-አቀፍ በሆኑ ግልጽ እቅዶች መመራት እንደሚገባ አሳስበዋል።
ዘጋቢ፡ ትዕግስቱ ጴጥሮስ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
የሕዝባችንን የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ የመመለስና ሜጋ ፕሮጀክቶችን በፍጥነት የማጠናቀቅ ቁርጠኝነታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
ሞዴል የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን መሠረተ ልማት ማሟላትና ምቹ የመማሪያ ከባቢን ለልጆች መፍጠር ለቀጣዩ የትምህርት ደረጃዎች መሠረት መሆኑ ተገለጸ
በጎፋ ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥና ጥራትና ተዓማኒነት ያለው የፍትህ አገልግሎት በመስጠት ረገድ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን የዞኑ ፍትህ መምሪያ አስታወቀ