የሴቶችን ተሳትፎ ማሳደግና አካታች በሆኑ እቅዶች መመራት እንደሚገባ ተገለጸ
ሀዋሳ፡ ነሐሴ 07/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሴቶችን ተሳትፎ ማሳደግና አካታች በሆኑ እቅዶች መመራት እንደሚገባ በካፋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ረዳት የመንግስት ተጠሪና የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወይዘሮ ጽዮን ታዬ ገለጹ።
ኃላፊዋ ይህንን የገለጹት የፓርቲውን የ2018 በጀት ዓመት የተግባር ዕቅድ ባቀረቡበት መድረክ ነው።
በአመራሮችና በአባላቱ ዘንድ የብልጽግናን እሳቤ በማስረጽና የአቅም ግንባታ ስራዎች ላይ በማተኮር የፓርቲውን አደረጃጀት ለማሳደግ ይሰራል ብለዋል።
ሀገር-አቀፍና ዓለም-አቀፍ ነባራዊ ሁኔታዎችን በመገንዘብና በእውቀት ላይ የተመሠረተ የአሰራር ስርዓትን በመዘርጋት ተግባራትን መከወን አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።
በፓርቲው ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ የተቀመጡ የውሳኔ አቅጣጫዎችን መነሻ በማድረግ የመልካም አስተዳደር ስራዎች በህዝብ ተሳትፎ እንዲጎለብቱ ይሰራል ብለዋል።
የሴቶችን ተሳትፎ በማሳደግ አካታች፣ አሳታፊ እና ሁሉን-አቀፍ በሆኑ ግልጽ እቅዶች መመራት እንደሚገባ አሳስበዋል።
ዘጋቢ፡ ትዕግስቱ ጴጥሮስ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
በጎፋ ዞን ዛላ ወረዳ ከ13 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባ ንጹህ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ ተጠናቆ ተመረቀ
በሀድያ ዞን ሌሞ ወረዳ ከ5 ሺህ 9 መቶ በላይ ተማሪዎች ክልላዊና ሀገር አቀፍ ብሔራዊ ፈተና ለመውሰድ ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸው ተገለፀ
”ከተረጅነት ወደ ምርታማነት” በሚል መሪ ሃሳብ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በሀዋሳ ከተማ የውይይት መድረክ በመካሄድ ላይ ነው