የሴቶችን ተሳትፎ ማሳደግና አካታች በሆኑ እቅዶች መመራት እንደሚገባ ተገለጸ
ሀዋሳ፡ ነሐሴ 07/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሴቶችን ተሳትፎ ማሳደግና አካታች በሆኑ እቅዶች መመራት እንደሚገባ በካፋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ረዳት የመንግስት ተጠሪና የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወይዘሮ ጽዮን ታዬ ገለጹ።
ኃላፊዋ ይህንን የገለጹት የፓርቲውን የ2018 በጀት ዓመት የተግባር ዕቅድ ባቀረቡበት መድረክ ነው።
በአመራሮችና በአባላቱ ዘንድ የብልጽግናን እሳቤ በማስረጽና የአቅም ግንባታ ስራዎች ላይ በማተኮር የፓርቲውን አደረጃጀት ለማሳደግ ይሰራል ብለዋል።
ሀገር-አቀፍና ዓለም-አቀፍ ነባራዊ ሁኔታዎችን በመገንዘብና በእውቀት ላይ የተመሠረተ የአሰራር ስርዓትን በመዘርጋት ተግባራትን መከወን አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።
በፓርቲው ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ የተቀመጡ የውሳኔ አቅጣጫዎችን መነሻ በማድረግ የመልካም አስተዳደር ስራዎች በህዝብ ተሳትፎ እንዲጎለብቱ ይሰራል ብለዋል።
የሴቶችን ተሳትፎ በማሳደግ አካታች፣ አሳታፊ እና ሁሉን-አቀፍ በሆኑ ግልጽ እቅዶች መመራት እንደሚገባ አሳስበዋል።
ዘጋቢ፡ ትዕግስቱ ጴጥሮስ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
የኤሌክትሪክ አገልግሎትን ፍትሀዊ በሆነ መልኩ ተደራሽ ለማድረግና በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ድጋፍ ወሳኝ ነው – አቶ መዝረዲን ሁሴን
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት ማጠቃለያና የቀጣይ አምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ ላይ የሚመክር ጉባኤ በሆሳዕና ከተማ እያካሄደ ነው
ታላቁ የጊፋታ ዋዜማ የሩጫ ውድድር በወላይታ ሶዶ ከተማ ተካሄደ