የተፈጥሮ መስህቦችን ለጎብኚዎች ምቹ ለማድረግ እየተደረገ ያለው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የሸካ ዞን አስተዳደር አስታወቀ

የተፈጥሮ መስህቦችን ለጎብኚዎች ምቹ ለማድረግ እየተደረገ ያለው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የሸካ ዞን አስተዳደር አስታወቀ

‎በዓለም ቅርስነት ከተመዘገበው የሸካ ጥብቅ ደን ውስጥ 41 ፏፏቴዎች፣ 17 ዋሻዎችና 52 የማዕድን ውሃ (ሆራ) እንደሚገኙ የዞኑ አስተዳደር አስታውቋል።

‎በዞኑ ያሉትን የቱሪስት መዳራሻዎችን ለጎብኚዎች ምቹ በማድረግ ወደ ሀብት የመቀየሩ ስራ በ2018 በጀት ዓመት ትኩረት ተሰጥቶት እንደሚሰራ የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ ተናግረዋል።

‎በዓለም የትምህርት ሳይንስና ባህል ተቋም”UNESCO” ሀብትነት ከተመዘገበው የሸካ ጥብቅ ደን ውስጥ መስህቦች በቱሪስት መዳረሻነት መለየታቸውን አስተዳዳሪው ይፋ አድርገዋል።

‎በዞኑ አራት የደጋ ሐይቆች መኖራቸው የሚታወቅ ሲሆን ከእነሱም መካከል ከባህር ጠለል በላይ 2ሺህ 7መቶ ሜትር ከፍታ ላይ የሚገኘው የጋንዶዎቺ ሐይቅ ዋነኛውና ትልቁ ሲሆን፣ ሙርሌ ቁጥር 1እና ቁጥር 2 ፣ እንዲሁም ሾሺ ተጠቃሾች ናቸው።

‎የጋንዶዎቺ ሐይቅን ለጎበኚዎች ምቹ ለማድረግ በበጀት ዓመቱ በዞኑ የጋራ ዕቅድ 3 ነጥብ 1 ኪሎሜትር ከ 6 ሚለየን ብር በላይ በሆነ ወጪ መሰራቱን የተናገሩት ዋና አስተዳዳሪው ከመንገዱ ጫፍ እስከ ሐይቁ መዳረሻ በማሽን የማይቆፈረውን ቦታ በመሃንዲሶች ምክረ-ሃሳብ መወጣጫ መንገዶችን በመስራት የተለያዩ ባለሀብቶችን በመሳብ ሎጆችን የመስራት ዕቅድ መያዙንም ገልጸዋል።

‎በ2018 በጀት ዓመት በእነዚህ ሀብቶች ላይ በትኩረት ለመስራት በዞኑ ያሉት ወረዳዎች ማህበረሰቡን በማስተባበር የመንገድ መዳረሻዎችን እንዲሰሩ የአሰራር ስርዓት ይዘረጋል ብለዋል።

‎የአካባቢው ወጣቶችና የማህበረሰብ አንቂዎች የጀመሩትን የሀገር ሀብት የማስተዋወቅ ስራ አጠናክረው እንዲቀጥሉና ያለውን ሀብት የማወቅና የማስተዋወቅ ልምድ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ዋና አስተዳዳሪ ጥሪ አስተላልፈዋል።

‎ዘጋቢ፡ ካሳሁን ደንበሎ – ከማሻ ጣቢያችን