በኮንሶ ዞን የከና ወረዳ -ደበና -ከመሌ የ 7 ነጥብ 54 ኪሎ ሜትር መንገድ ግንባታ በይፋ ተጀመረ
ሀዋሳ፡ ነሐሴ 05/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በ40 ሚሊየን ብር ወጪ የሚገነባው የኮንሶ ዞን ከና ወረዳ -ደበና -ከመሌ የ 7 ነጥብ 54 ኪሎ ሜትር መንገድ ግንባታ በይፋ ተጀምሯል።
የመንገድ ግንባታው መጀመር ያመረቱትን ምርት ለገበያ ከማቅረብ ባሻገር የህዝብ ለህዝብ ትስስርን በማጠናከር ያለው ፋይዳ ላቅ ያለ መሆኑን ነዋሪዎች አረጋግጠዋል።
በኮንሶ ዞን የከና ወረዳ ነዋሪዎች መካከል አቶ ከፋይ ገብሬና ገዛኸኝ ገሌቦ እንዳሉት የዘመናት ጥያቄ የነበረውን የመንገድ መሠረተ ልማት ምላሽ በመስጠት መንግስት ያደረገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን ጠቁመዋል።
የመንገድ መሠረተ ልማቱ ሲጠናቀቅ ያመረትነውን ምርት ገበያ በማድረስ ተጠቃሚ ከመሆናቸውም ባሻገር የህዝብ ለህዝ ትስስርን እንደሚያጠናክር ነዋሪዎቹ ገልፀዋል ።
በዚህ ወቅት መልዕክት ያስተላለፉት የከና ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ካርሾ ገዴኖ፥ የገጠር የመንገድ ትስስር ለምግብ ዋስትና ፕሮግራም እና ለአከባቢው ነዋሪ ብሎም ለአርሶአደሩ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል ።
መንገዱ በርካታ ቀበሌያትን በማስተሳሰር በአከባቢው ለውጥ እንዲመዘገብ የሚያደርግ በመሆኑ ህብረተሰቡ ለመንገዱ ግንባታ የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ ያስተላለፉት ደግሞ የኮንሶ ዞን መንገድና ትራንስፖርት ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሰለሞን ካሊታ ናቸው ።
የኮንሶ ዞን ም/አስተዳዳሪ እና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ጉራሾ ጎስኬ የመንገድ ጥያቄ ረጅም ጊዜ የመልካም አስተዳደር ጥያቄ እንደነበር አስታውሰው፥ መንግስት ባደረገው ጥረት የህዝቡን የመሠረተ ልማት ጥያቄ ደረጃ በደረጃ በመመለሱ ደስተኛ ሆነናል ብለዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊና የትራንስፖርት ዘርፍ ኃላፊ ብርሃኑ ጌቦ (ዶ/ር) ቢሮው ከአለም ባንክ ጋር በመተባበር በ40 ሚሊየን ብር ወጪ የመንገድ ግንባታውን መጀመሩን ተናግረዋል።
ከዚህ ቀደም የተገነቡትን የማስተካከል እና 7 ነጥብ 54 ኪሎ ሜትር ጠረጋ እንደሚደረግ ጠቁመው፥ ይህም ለወረዳው ያለው ፋይዳ ዘርፈ ብዙ እንደሆነ ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡ ተመኙህ ገረሱ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ