የምዕራብ ኦሞ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 12ኛ ዓመት የስራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ጉባኤ በጀሙ ከተማ እያካሄደ ይገኛል
ጉባኤውን በንግግር የከፈቱት የዞኑ ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ቢልልኝ ወልደሰንበት እንደተናገሩት፤ ምክር ቤቶች የህዝብ ሉዓላዊነት መገለጫ በመሆናቸው የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ሚናዎችን እየተወጡ ይገኛሉ።
በበጀት ዓመቱ ያለአግባብ የባከኑ የመንግስት ሀብትና ንብረት እንዲመለሱ እና የአሰራር ጥሰቶች እንዲታረሙ በተሰራው ስራ አመርቂ ውጤት በመመዝገቡ በቀጣይም ልዩ ትኩረት በመስጠት ይሰራል ብለዋል።
ዋና አፈ ጉባኤው አክለውም በሀገራችን የተጀመረውን የብልፅግና ጉዞ ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር ምክር ቤቱ ሰው ሰራሽም ሆነ ተፈጥሮአዊ ችግሮችን በመቅረፍ ስኬታማ እንዲሆን ሊረባረቡ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።
ምክር ቤቱ በ2 ቀን ውሎው የ3ቱም የመንግስት አካላት የ2017 ዓ.ም ዕቅድ አፈፃፀም፣ የ2018 ጠቋሚ ዕቅድ እና የ2018 የዞኑ በጀት ቀርቦ እንደሚፀድቅ እንዲሁም የተለያዩ አጀንዳዎች ላይ እንደሚመክር እና የሹመት ስነ-ስርዓት እንደሚካሄድ ከመርሀ ግብሩ ለማውቅ ተችሏል።
በዞኑ ምክር ቤት ጉባኤ ላይ የህዝብ ተወካዮችና የክልል ምክር ቤት አባላት እንዲሁም የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል።
ዘጋቢ፡ ዮናስ ወ/ገብርኤል – ከሚዛን ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ