የምዕራብ ኦሞ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 12ኛ ዓመት የስራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ጉባኤ በጀሙ ከተማ እያካሄደ ይገኛል
ጉባኤውን በንግግር የከፈቱት የዞኑ ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ቢልልኝ ወልደሰንበት እንደተናገሩት፤ ምክር ቤቶች የህዝብ ሉዓላዊነት መገለጫ በመሆናቸው የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ሚናዎችን እየተወጡ ይገኛሉ።
በበጀት ዓመቱ ያለአግባብ የባከኑ የመንግስት ሀብትና ንብረት እንዲመለሱ እና የአሰራር ጥሰቶች እንዲታረሙ በተሰራው ስራ አመርቂ ውጤት በመመዝገቡ በቀጣይም ልዩ ትኩረት በመስጠት ይሰራል ብለዋል።
ዋና አፈ ጉባኤው አክለውም በሀገራችን የተጀመረውን የብልፅግና ጉዞ ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር ምክር ቤቱ ሰው ሰራሽም ሆነ ተፈጥሮአዊ ችግሮችን በመቅረፍ ስኬታማ እንዲሆን ሊረባረቡ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።
ምክር ቤቱ በ2 ቀን ውሎው የ3ቱም የመንግስት አካላት የ2017 ዓ.ም ዕቅድ አፈፃፀም፣ የ2018 ጠቋሚ ዕቅድ እና የ2018 የዞኑ በጀት ቀርቦ እንደሚፀድቅ እንዲሁም የተለያዩ አጀንዳዎች ላይ እንደሚመክር እና የሹመት ስነ-ስርዓት እንደሚካሄድ ከመርሀ ግብሩ ለማውቅ ተችሏል።
በዞኑ ምክር ቤት ጉባኤ ላይ የህዝብ ተወካዮችና የክልል ምክር ቤት አባላት እንዲሁም የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል።
ዘጋቢ፡ ዮናስ ወ/ገብርኤል – ከሚዛን ጣቢያችን

More Stories
የኤሌክትሪክ አገልግሎትን ፍትሀዊ በሆነ መልኩ ተደራሽ ለማድረግና በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ድጋፍ ወሳኝ ነው – አቶ መዝረዲን ሁሴን
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት ማጠቃለያና የቀጣይ አምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ ላይ የሚመክር ጉባኤ በሆሳዕና ከተማ እያካሄደ ነው
ታላቁ የጊፋታ ዋዜማ የሩጫ ውድድር በወላይታ ሶዶ ከተማ ተካሄደ