የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚሰሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ተገለፀ
ሀዋሳ፡ ነሐሴ 05/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የክረምት ወራት የውክልና ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚሰሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለባቸው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክርቤት ገለፀ፡፡
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ከመረጣቸው ህዝብ ጋር በቀጣይ መወያየት እንደሚጀምሩ ተጠቁሟል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክርቤት በ2017 በጀት አመት የፓርላማ እና የክልል ምክር ቤት አባላት የክረምት ወራት ዉክልና ስራዎች ማስጀመሪያ ምክክርና የኦሬንተሽን መድረክ በአርባምንጭ ከተማ እየተካሄደ ነው።
መድረኩን በንግግር የከፈቱት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክርቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባዉዲ በልማት የመልካም አስተዳደር የሚነሱ ጥያቄዎችን በማጤን ምላሾችን በመስጠት መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል ።
የህዝቡን ጥያቄ በማዳመጥ ተገቢውን ምላሽና ማብራሪያ መስጠት ቀዳሚ ተግባር እንደሆነ የገለፁት ደግሞ በኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፓርላማ አባልና የልዕኩ ተወካይ አቶ መለሰ መና ናቸዉ።
በመድረኩም በክረምት ወራት የፓርላማ አባት ወደየክልል ምርጫ ቦታቸው ሲመለሱ የማህበረሰብ ንቅናቄዎች፣ ዘላቂ ሰላምን ከማስፈን አኳያ፣ የኢኮኖሚ ልማት፣ የመልካም አስተዳደርና የአገልግሎት አሰጣጥ እና መሰል ስራዎች እንደሚደግፉ በቀረበው ሰነድ ተገልጿል ።
በ2017 በጀት አመት በክልሉ በህዝብ ለተነሱት ጥያቄዎች የተሰጡ ምላሾችን የርዕሰ መስተዳድር ልዩ አማካሪ ዶ/ር ቦሻ ቦምቤ እያቀረቡ ይገኛሉ ።
በመድረኩም የፓርላማ አባላት የዞን አፈጉባኤዎች ጨምሮ አስፈፃሚ አካላት እየተሳተፉ ይገኛሉ ።
ዘጋቢ፡ ስምረት አስማማው – አርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር እንዲኖር የተለያዩ ፕሮጀክቶች መዘጋጀታቸው ተገለጸ
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላማዊ መንገድ እንዲጠናቀቅ የሁሉም የክልሉ ነዋሪ ሚና ከፍተኛ ነበር – ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)
ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ የአርባምንጭ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከልን መርቀው ከፈቱ