ክሪስታል ፓላስ የኮሙዩኒቲ ሽልድ ዋንጫ ሻምፒዮን ሆነ
ሀዋሳ: ነሐሴ 04/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ክሪስታል ፓላስ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ሊቨርፑልን በመለያ ምት በማሸነፍ የኮሙዩኒቲ ሽልድ ዋንጫን አሸናፊ ሆኗል።
ከፍተኛ ፉክክር በታየበትና በዌምብሌይ ስታዲየም በተደረገው የፍፃሜ ጨዋታ ክሪስታል ፓላስ ሊቨርፑልን በማሸነፍ ዋንጫውን አንስቷል።
ሁለቱ ቡድኖች በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ባደረጉት ፍልሚያ 2 ለ 2 በሆነ አቻ ውጤት ሲያጠናቅቁ÷ የሊቨርፑልን ግቦች አዲስ ፈራሚዎቹ ሁጎ ኢኪቴኪ እና ጀረሚ ፍሪምፖንግ አስቆጥረዋል፡፡
የክሪስታል ፓላስን ሁለቱን ግቦች ማቴታ እና ኢስማኢል ሳር አስቆጥረዋል።
ጨዋታው በሁት አቻ ውጤት መጠናቀቁን ተከትሎ ወደ መለያ ምት ያመሩት ቡድኖች ክሪስታል ፓላስ በመለያ ምት ሊቨርፑልን 3 ለ 2 በማሸነፍ ሻምፒዮን ሆኗል።

More Stories
አርሰናል በአስቶንቫላ ተሸነፈ
ኮቢ ሜይኑ ማንቸስተር ዩናይትድን መልቀቅ ይፈልጋል
በመላ አፍሪካ ርዕሰ ከተሞች መካከል፣ ለዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲና የጋራ አህጉራዊ ተቋማት ማዕከል በሆነችው ምድራችን፣ ታላቅ የሚዲያ መድረክ ማስተናገድ ታላቅ ኩራት ነው – የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት