በሁሉም የትምህርት ስራዎች የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ባለድርሻ አካላት በቁርጠኝነት ሊንቀሳቀሱ ይገባል ሲል የቤንች ሸኮ ዞን አስተዳደር አሳሰበ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 30/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በዞኑ በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሁሉም የትምህርት ስራዎች የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ባለድርሻ አካላት በቁርጠኝነት ሊንቀሳቀሱ ይገባል ሲል የቤንች ሸኮ ዞን አስተዳደር አሳስቧል፡፡
የዞኑ ትምህርት መምሪያ “የጋራ እርብርብ ለላቀ የትምህርት ጥራት” በሚል መሪ ቃል የ2018 ዓ/ም የትምህርት ሥራዎች ንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው።
የቤንች ሸኮ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የዞኑ ከተማ ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ መስፍን መንገሻ እንደተናገሩት ትምህርት ለአንድ ሀገር ዘላቂነት ያለው ዕድገትና ልማት ለማስመዝገብ ወሳኝ ነው ብለዋል።
በዞኑ በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሁሉም የትምህርት ስራዎች የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ባለድርሻ አካላት በቁርጠኝነት ሊንቀሳቀሱ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
በተለይ በትምህርት ዘመኑ የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል የሚያስችሉ ስራዎችን በተደራጀ መልኩ መስራት እንደሚገባም መክረዋል።
የዞኑ ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ አገኘሁ ወርቁ እንደገለፁት ዛሬ በአለማችን ያደጉና በስልጣኔ ማማ የሚገኙ ሀገራቶች ዋነኛው ሚስጥር ለትምህርት በሰጡት ትኩረት ነው ብለዋል።
በተለይ የትምህርት ስራ የባለድርሻ አካላት ቅንጅትና ተሳትፎ የሚጠይቅ በመሆኑ በየደረጃው የሚገኙ የትምህርት ባለድርሻ አካላት የነቃ ተሳትፎ ሊያደርጉ እንደሚገባም ጠቁመዋል።
የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመኑን ስኬታማ ለማድረግ ከባለፈው የትምህርት ዘመን የነበሩ ድክመቶችን አርመን ጥንካሬን አጎልብተን ማስቀጠል ይገባናል ብለዋል።
በመድረኩ ላይ በመምሪያው የትምህርት ቤቶች ማሻሻል ዳይሬክቶሬት ቡድን መሪ አቶ ጌታሁን ቢኒያም የበጀት አመቱን ዕቅድ አፈጻጸም በተመለከተ በዝርዝር ሪፖርት አቅርበዋል።
በመድረኩ ላይ ከክልል ከዞንና ከወረዳ የተውጣጡ አመራሮች የትምህርት ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ተሳታፊዎች ሆነዋል
ዘጋቢ፡ ጦያር ይማም – ከሚዛን ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል