የካፋ ዞን ፖሊስ መምሪያ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምን እየገመገመ ነው
መድረኩ በመምሪያው የስራ አፈፃፀም ላይ በመወያየት የተሻሉ ልምዶችን ለማጎልበትና ጉድለቶችን ለማረም የሚያስችል ሀሳብና አቅጣጫ የሚመላከትበት ነው ተብሏል።
በ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ምክክር ተደርጎ የሚጸድቅ ሲሆን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች የእውቅና መርሐ-ግብር እንደሚከናወን ከወጣው ፕሮግራም መረዳት ተችሏል።
በመድረኩ ባለፈው በጀት ዓመት የተከናወኑ አበይት ተግባራትን የሚያስቃኝ የፎቶ ኤግዝቢሽን ተዘጋጅቷል።
በውይይት መድረኩ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፣ የካፋ ዞን፣ የወረዳዎችና የከተማ አስተዳደሮች የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ አሳምነው አትርሳው – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ