የካፋ ዞን ፖሊስ መምሪያ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምን እየገመገመ ነው
መድረኩ በመምሪያው የስራ አፈፃፀም ላይ በመወያየት የተሻሉ ልምዶችን ለማጎልበትና ጉድለቶችን ለማረም የሚያስችል ሀሳብና አቅጣጫ የሚመላከትበት ነው ተብሏል።
በ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ምክክር ተደርጎ የሚጸድቅ ሲሆን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች የእውቅና መርሐ-ግብር እንደሚከናወን ከወጣው ፕሮግራም መረዳት ተችሏል።
በመድረኩ ባለፈው በጀት ዓመት የተከናወኑ አበይት ተግባራትን የሚያስቃኝ የፎቶ ኤግዝቢሽን ተዘጋጅቷል።
በውይይት መድረኩ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፣ የካፋ ዞን፣ የወረዳዎችና የከተማ አስተዳደሮች የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ አሳምነው አትርሳው – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ