የካፋ ዞን ፖሊስ መምሪያ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምን እየገመገመ ነው
መድረኩ በመምሪያው የስራ አፈፃፀም ላይ በመወያየት የተሻሉ ልምዶችን ለማጎልበትና ጉድለቶችን ለማረም የሚያስችል ሀሳብና አቅጣጫ የሚመላከትበት ነው ተብሏል።
በ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ምክክር ተደርጎ የሚጸድቅ ሲሆን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች የእውቅና መርሐ-ግብር እንደሚከናወን ከወጣው ፕሮግራም መረዳት ተችሏል።
በመድረኩ ባለፈው በጀት ዓመት የተከናወኑ አበይት ተግባራትን የሚያስቃኝ የፎቶ ኤግዝቢሽን ተዘጋጅቷል።
በውይይት መድረኩ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፣ የካፋ ዞን፣ የወረዳዎችና የከተማ አስተዳደሮች የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ አሳምነው አትርሳው – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል