በጎፋ ዞን የደምባ ጎፋ ወረዳ ሕዝብ ምክር ቤት 4ኛ ዙር 3ኛ መደበኛ ጉባኤ እየተካሄደ ነው
በጉባኤው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የደምባ ጎፋ ወረዳ ህዝብ ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ አበበ አማኔ ባስተላለፉት መልዕክት ምክር ቤቶች የሕዝብ ሉአላዊ የስልጣን ባለቤት መገለጫ በዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታና በመንግስት አሠራር የሕዝብ ተሳትፎ የሚረጋገጥባቸው መሆናቸውን ገልጸዋል።
ምክር ቤቱ በሕገ-መንግስቱ የተሰጠውን ስልጣን በመጠቀም የሕዝቡን የመልካም አሰተዳደር እና የወጣቶች ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በመከታተልና በመቆጣጠር የተሻለ አፈፃፀም እንዲመዘገብ እየተጋ ይገኛል ብለዋል።
ጉባኤው በዛሬው ውሎ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርትና የቀጣይ ዓመት ጠቋሚ ዕቅድ እንዲሁም ልዩ ልዩ አጀንዳዎች ቀርበው ይፀድቃሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በጉባኤው የጎፋ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ አበበች መርጊያ፣ የደምባ ጎፋ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አንዳርጌ አራታ፣ የደምባ ጎፋ ወረዳ የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ሰማዬ ሻምበል፣ የደምባ ጎፋ ወረዳ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አበበ አማኔ ጨምሮ የወረዳው አጠቃላይ አመራሮች የወረዳው የምክር ቤት አባላት እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ስንታየሁ ሙላቱ – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ