በጎፋ ዞን የደምባ ጎፋ ወረዳ ሕዝብ ምክር ቤት 4ኛ ዙር 3ኛ መደበኛ ጉባኤ እየተካሄደ ነው
በጉባኤው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የደምባ ጎፋ ወረዳ ህዝብ ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ አበበ አማኔ ባስተላለፉት መልዕክት ምክር ቤቶች የሕዝብ ሉአላዊ የስልጣን ባለቤት መገለጫ በዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታና በመንግስት አሠራር የሕዝብ ተሳትፎ የሚረጋገጥባቸው መሆናቸውን ገልጸዋል።
ምክር ቤቱ በሕገ-መንግስቱ የተሰጠውን ስልጣን በመጠቀም የሕዝቡን የመልካም አሰተዳደር እና የወጣቶች ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በመከታተልና በመቆጣጠር የተሻለ አፈፃፀም እንዲመዘገብ እየተጋ ይገኛል ብለዋል።
ጉባኤው በዛሬው ውሎ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርትና የቀጣይ ዓመት ጠቋሚ ዕቅድ እንዲሁም ልዩ ልዩ አጀንዳዎች ቀርበው ይፀድቃሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በጉባኤው የጎፋ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ አበበች መርጊያ፣ የደምባ ጎፋ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አንዳርጌ አራታ፣ የደምባ ጎፋ ወረዳ የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ሰማዬ ሻምበል፣ የደምባ ጎፋ ወረዳ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አበበ አማኔ ጨምሮ የወረዳው አጠቃላይ አመራሮች የወረዳው የምክር ቤት አባላት እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ስንታየሁ ሙላቱ – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል