በክልሉ ውስን ቦታዎች የታዩ የፀጥታ ችግሮች ዕልባት እያገኙ መጥተዋል – ዋና አፈ ጉባዔ ፋጤ ስርሞሎ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 29/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በክልሉ ውስን ቦታዎች የታዩ የፀጥታ ችግሮች ዕልባት እያገኙ መጥተዋል ሲሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባዔ ፋጤ ስርሞሎ ገለጹ፡፡
ክልሉን የወከሉ የፓርላማ አባላት እና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት አባላት በጋራ የህዝብ ውክልና ስራ ለማከናወን የሚያስችል የውይይት መድረክ በወልቂጤ ከተማ በማካሔድ ላይ ናቸው፡፡
ተመራጮች ወደ መረጣቸው ህዝብ ቀርበው ማወያየታቸው በመንግስትና በህዝብ መካከል ያለው ግንኙነት በማጠናከር ግልጽነትን ይፈጥራል ያሉት የክልሉ ህዝብ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባዔ ፋጤ ስርሞሎ፥ በ2017 የበጀት አመት በተከናወኑ የልማትና መልካም አስተዳደር ስራዎች በክልልና በፌደራል ሊሰሩ የሚገባቸውን ጥያቄዎችን በማሰባሰብ ምላሽ ማሰጠት ተችሏል ብለዋል፡፡
በክልሉ ውስን አከባቢዎች አጋጥመው የነበሩ የፀጥታ ሁኔታ መሻሻሉን የገለጹት ወይዘሮ ፋጤ፥ ይህ ለውጥ እንዲመጣና የአስፈፃሚው አካል የሚጠበቅበትን እንዲወጣ የምክር ቤት አባላት ያደረጉት ክትትልና ድጋፍ ድርሻው ላቅ ያለ መሆኑን ዋና አፈ ጉባዔዋ አንስተዋል፡፡
በያዝነው የክረምት ወቅት የምክር ቤት አባላት ወደተመረጡበት አከባቢ በመሄድ በመንግስት የተከናወኑ ተግባራትን በመመልከት በህዝብ የሚነሱ ሃሳቦችን ይዞ በመመለስ ከአስፈፃሚው አካል ጋር በቀጣይ ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ: ሲሳይ ደበበ
በክልሉ ውስን ቦታዎች የታዩ የፀጥታ ችግሮች ዕልባት እያገኙ መጥተዋል – ዋና አፈ ጉባዔ ፋጤ ስርሞሎ

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል