የሚዛን አማን ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት በበጀት አመቱ ከማህበረሰቡ በመቀናጀት የከተማዋን ሠላምና ፀጥታ ለማስከበር ከፍተኛ ስራ መስራቱን ገለጸ
የሚዛን አማን ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት የ2017ዓ.ም ዕቅድ አፈጻጸም መድረክ አካሂዷል።
የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጅነር ሰለሞን ለዊ እንደተናገሩት ከተማዋ ከጊዜ ወደ ጊዜ ፈጣን የሆነ ዕድገት እያሳች መሆኑን ተናግረዋል
በዚህም የከተማውን ዕድገት ተከትሎ የሚፈፀሙ ወንጀሎች ለመከላከልና ያለውን ሠላምና ፀጥታ ይበልጥ ለማስጠበቅ የከተማው ፖሊስ ከፍተኛ ሚና ነበረው ብለዋል፡፡
በተለይ በከተማዋ የተጀመረውን የልማት ስራዎች ከዳር ማድረስ የሚቻለው በእጃችን ያለውን ሠላም ማስጠበቅ ስንችል ያሉት ከንቲባው ፖሊስ ማህበረሰቡን በማሳተፍ የጀመረውን አመርቂ ስራ በቀጣይ አጠናክሮ ማስቀጠል አለበት ብለዋል።
የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ምናሉ ታደሰ እንደገለፁት በበጀት አመቱ ፖሊስ ከማህበረሰቡ በመቀናጀት የከተማዋን ሠላምና ፀጥታ ለማስከበር ከፍተኛ ስራ መስራቱን ተናግረዋል
በበጀት አመቱ በከተማዋ 344 የተለያዩ የወንጀል ድርጊቶች የተፈፀሙ ሲሆን በባለፈው በጀት አመት ከነበረው አንፃር በ230 ወንጀሎች መቀነስ አሳይቷል ብለዋል።
የከተማው ሠላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አስማረ ቶቲ በበኩላቸው የከተማው ህዝብ ለሠላሙ ከፀጥታ መዋቅር ጎን በመሰለፍ እያሳየ ያለው በጎ ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።
በመድረኩ ላይ የከተማው አመራሮች የሀይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች እንዲሁም የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተሳታፊዎች ሆነዋል።
ዘጋቢ፡- ጦያር ይማም ከሚዛን ቅርንጫፍ

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል