ከ300 ሚሊዮን ብር በላይ በወልቂጤ ከተማ የሚገነባው የአትሌት ሰለሞን ባረጋ ሎጅ የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ
ሎጁ የአካባቢውን ገጽታ በመቀየርና ለበርካቶች የሥራ እድል በመፍጠር ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረውም ተገልጿል።
በመርሃግብሩ ላይ የተገኙት የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ ሎጁ የአካባቢውን ገጽታ በመቀየርና ለበርካቶች የሥራ እድል በመፍጠር ከፍተኛ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።
ለአትሌት ሰለሞን ባረጋ በሽልማት በተበረከተለት በ15 ሺህ ካሬ ቦታ ላይ የሚገነባው ሎጁ ከሁለት እስከ ሦስት ዓመት ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ተጠቁሟል።
የወልቂጤ ከተማ ከንቲባ አቶ ሙራድ ከድር የወልቂጤ ከተማን ለማልማት ለተጀመረው እንቅስቃሴ የሎጁ መገንባት ትልቅ ሚና አለው ብለዋል።
በተቀመጠው ጊዜ ተጠናቅቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ከተማ አስተዳደሩ ድጋፍ እንደሚያደርግም ጠቁመዋል።
አትሎት ሰለሞን ባረጋ በበኩሉ አካባቢውን ለማልማት ካለው ቁጭት በመነሳት ወደ ልማቱ መግባቱንና በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ለአገልግሎት እንዲበቃ የአካባቢው ማህበረሰብ በባለቤትነት እንዲያግዘው ጠይቋል።
ደረጃውን የጠበቀና ባለ አምስት ኮከብ ሎጅ ግንባታ ከ300 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚፈጅ ተጠቁሟል።
ዘጋቢ፣ ተረፈ ሀብቴ

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ