ከ300 ሚሊዮን ብር በላይ በወልቂጤ ከተማ የሚገነባው የአትሌት ሰለሞን ባረጋ ሎጅ የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ
ሎጁ የአካባቢውን ገጽታ በመቀየርና ለበርካቶች የሥራ እድል በመፍጠር ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረውም ተገልጿል።
በመርሃግብሩ ላይ የተገኙት የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ ሎጁ የአካባቢውን ገጽታ በመቀየርና ለበርካቶች የሥራ እድል በመፍጠር ከፍተኛ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።
ለአትሌት ሰለሞን ባረጋ በሽልማት በተበረከተለት በ15 ሺህ ካሬ ቦታ ላይ የሚገነባው ሎጁ ከሁለት እስከ ሦስት ዓመት ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ተጠቁሟል።
የወልቂጤ ከተማ ከንቲባ አቶ ሙራድ ከድር የወልቂጤ ከተማን ለማልማት ለተጀመረው እንቅስቃሴ የሎጁ መገንባት ትልቅ ሚና አለው ብለዋል።
በተቀመጠው ጊዜ ተጠናቅቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ከተማ አስተዳደሩ ድጋፍ እንደሚያደርግም ጠቁመዋል።
አትሎት ሰለሞን ባረጋ በበኩሉ አካባቢውን ለማልማት ካለው ቁጭት በመነሳት ወደ ልማቱ መግባቱንና በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ለአገልግሎት እንዲበቃ የአካባቢው ማህበረሰብ በባለቤትነት እንዲያግዘው ጠይቋል።
ደረጃውን የጠበቀና ባለ አምስት ኮከብ ሎጅ ግንባታ ከ300 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚፈጅ ተጠቁሟል።
ዘጋቢ፣ ተረፈ ሀብቴ

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል