ከ300 ሚሊዮን ብር በላይ በወልቂጤ ከተማ የሚገነባው የአትሌት ሰለሞን ባረጋ ሎጅ የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ
ሎጁ የአካባቢውን ገጽታ በመቀየርና ለበርካቶች የሥራ እድል በመፍጠር ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረውም ተገልጿል።
በመርሃግብሩ ላይ የተገኙት የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ ሎጁ የአካባቢውን ገጽታ በመቀየርና ለበርካቶች የሥራ እድል በመፍጠር ከፍተኛ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።
ለአትሌት ሰለሞን ባረጋ በሽልማት በተበረከተለት በ15 ሺህ ካሬ ቦታ ላይ የሚገነባው ሎጁ ከሁለት እስከ ሦስት ዓመት ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ተጠቁሟል።
የወልቂጤ ከተማ ከንቲባ አቶ ሙራድ ከድር የወልቂጤ ከተማን ለማልማት ለተጀመረው እንቅስቃሴ የሎጁ መገንባት ትልቅ ሚና አለው ብለዋል።
በተቀመጠው ጊዜ ተጠናቅቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ከተማ አስተዳደሩ ድጋፍ እንደሚያደርግም ጠቁመዋል።
አትሎት ሰለሞን ባረጋ በበኩሉ አካባቢውን ለማልማት ካለው ቁጭት በመነሳት ወደ ልማቱ መግባቱንና በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ለአገልግሎት እንዲበቃ የአካባቢው ማህበረሰብ በባለቤትነት እንዲያግዘው ጠይቋል።
ደረጃውን የጠበቀና ባለ አምስት ኮከብ ሎጅ ግንባታ ከ300 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚፈጅ ተጠቁሟል።
ዘጋቢ፣ ተረፈ ሀብቴ

More Stories
ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የእርስ በርስ ግንኙነትና አንድነትን የሚያጠናክር ተግባር መሆኑ ተገለጸ
በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል አለባቸዉ – ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ
የሕዝባችንን የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ የመመለስና ሜጋ ፕሮጀክቶችን በፍጥነት የማጠናቀቅ ቁርጠኝነታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)