ከማረምና ማነጽ ጎን ለጎን የሀገሪቱን አረንጓዴ ልማት እስትራቴጂን ለማሳካት ሚናውን እንደሚወጣ የጂንካ ማረሚያ ተቋም አስታወቀ
“በመትከል ማንሰራራት” በሚል መሪ ቃል የጂንካ ማረሚያ ተቋም ፖሊስ አባላትና ታራሚዎች የአንድ ጀንበር ችግኝ ተከላ አካሂደዋል።
የሚተከለውን ችግኝ በመንከባከብና ለአካባቢውና ለአለም አቀፍ አየር ንብረት ለውጥ እንዲሻሻል የተጀመረውን የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ በተጠናከረ መልኩ ይሰራል ያሉት የጂንካ ማራሚያ ተቋም አዛዥ ምክትል ኮማንደር አስቻለው ነሬሬ፡፡
በተቋሙ የግብርና ባለሙያ የሆኑት ወ/ሮ ብዙነሽ አገኘሁ፤ በማረሚያ ተቋሙ ለምግብነትና ለሌሎች አገልግሎቶች የሚውሉ ችግኞች እየተተከሉ መሆኑን ጠቁመው የጽድቀት መጠናቸውም በተሻለ ሁኔታ እንዲቀጥል ውሃ የማጠጣትና የመንከባከብ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
የጂንካ ማረሚያ ተቋምን ጨምሮ በኣሪ ዞን በአንድ ጀንበር 4 ሚሊዮን 201 ሺህ 452 በላይ ችግኝ እየተተከለ ይገኛል።
ዘጋቢ: ጄታ ታገሠ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል