ከማረምና ማነጽ ጎን ለጎን የሀገሪቱን አረንጓዴ ልማት እስትራቴጂን ለማሳካት ሚናውን እንደሚወጣ የጂንካ ማረሚያ ተቋም አስታወቀ
“በመትከል ማንሰራራት” በሚል መሪ ቃል የጂንካ ማረሚያ ተቋም ፖሊስ አባላትና ታራሚዎች የአንድ ጀንበር ችግኝ ተከላ አካሂደዋል።
የሚተከለውን ችግኝ በመንከባከብና ለአካባቢውና ለአለም አቀፍ አየር ንብረት ለውጥ እንዲሻሻል የተጀመረውን የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ በተጠናከረ መልኩ ይሰራል ያሉት የጂንካ ማራሚያ ተቋም አዛዥ ምክትል ኮማንደር አስቻለው ነሬሬ፡፡
በተቋሙ የግብርና ባለሙያ የሆኑት ወ/ሮ ብዙነሽ አገኘሁ፤ በማረሚያ ተቋሙ ለምግብነትና ለሌሎች አገልግሎቶች የሚውሉ ችግኞች እየተተከሉ መሆኑን ጠቁመው የጽድቀት መጠናቸውም በተሻለ ሁኔታ እንዲቀጥል ውሃ የማጠጣትና የመንከባከብ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
የጂንካ ማረሚያ ተቋምን ጨምሮ በኣሪ ዞን በአንድ ጀንበር 4 ሚሊዮን 201 ሺህ 452 በላይ ችግኝ እየተተከለ ይገኛል።
ዘጋቢ: ጄታ ታገሠ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የፃማኮ ብሄረሰብ የዘመን መለወጫ የ”ባርባይሳ” በዓል የህብረ ብሄራዊ አንድነት መገለጫ፣ የሰላምና የመተሳሰብ ምልክትነቱን በማግዘፍ ለዓለም አደባባይ ማብቃት ይገባል ሲሉ የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ገለጹ
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ