ከማረምና ማነጽ ጎን ለጎን የሀገሪቱን አረንጓዴ ልማት እስትራቴጂን ለማሳካት ሚናውን እንደሚወጣ የጂንካ ማረሚያ ተቋም አስታወቀ
“በመትከል ማንሰራራት” በሚል መሪ ቃል የጂንካ ማረሚያ ተቋም ፖሊስ አባላትና ታራሚዎች የአንድ ጀንበር ችግኝ ተከላ አካሂደዋል።
የሚተከለውን ችግኝ በመንከባከብና ለአካባቢውና ለአለም አቀፍ አየር ንብረት ለውጥ እንዲሻሻል የተጀመረውን የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ በተጠናከረ መልኩ ይሰራል ያሉት የጂንካ ማራሚያ ተቋም አዛዥ ምክትል ኮማንደር አስቻለው ነሬሬ፡፡
በተቋሙ የግብርና ባለሙያ የሆኑት ወ/ሮ ብዙነሽ አገኘሁ፤ በማረሚያ ተቋሙ ለምግብነትና ለሌሎች አገልግሎቶች የሚውሉ ችግኞች እየተተከሉ መሆኑን ጠቁመው የጽድቀት መጠናቸውም በተሻለ ሁኔታ እንዲቀጥል ውሃ የማጠጣትና የመንከባከብ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
የጂንካ ማረሚያ ተቋምን ጨምሮ በኣሪ ዞን በአንድ ጀንበር 4 ሚሊዮን 201 ሺህ 452 በላይ ችግኝ እየተተከለ ይገኛል።
ዘጋቢ: ጄታ ታገሠ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ