ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ነገ ሐምሌ 24/2017 “በመትከል ማንሰራራት” በሚል መሪ ሀሳብ በሚካሔደው የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ላይ የክልሉ ህዝብ የላቀ ተሳትፎ እንዲያደርግ ጥሪ አቀረቡ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ነገ ሐምሌ 24/2017 “በመትከል ማንሰራራት” በሚል መሪ ሀሳብ በሚካሔደው የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ላይ የክልሉ ህዝብ የላቀ ተሳትፎ እንዲያደርግ ጥሪ አቀረቡ፡፡
በአገር አቀፍ ደረጃ 700 ሚሊዮን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ደግሞ 6 ነጥብ 8 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀንበር መትከል የሚያስችል ዝግጅት መጠናቀቁን ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።
ይህን ሀገራዊ ጥሪ ከግብ ለማድረስ የክልሉ ህዝብ በነቂስ በመውጣት አሻራውን ማሳረፍ እንዳለበት ርዕሰ መስተዳድሩ ጥሪ ማቅረባቸውን የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመለክታል።

More Stories
በግብርናው ኢኮኖሚ ዘርፍ ትልቅ ፋይዳ እያስገኘ ያለውን የእንስሳት ሀብት ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ በትኩረት እየተሠራ ነው – የእንስሳትና ዓሣ ሀብት ልማት ዘርፍ ኃላፊ ዶ/ር መሠረት አበራ
የቡና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ የኣሪ ዞን ግብርና መምሪያ ቡናና ቅመማ ቅመም ጽህፈት ቤት አሰታወቀ
በሀገሪቱ ያለው 80 በመቶ ቡና ያረጀ በመሆኑ መታደስ እንደሚገባ ተጠቆመ