ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ነገ ሐምሌ 24/2017 “በመትከል ማንሰራራት” በሚል መሪ ሀሳብ በሚካሔደው የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ላይ የክልሉ ህዝብ የላቀ ተሳትፎ እንዲያደርግ ጥሪ አቀረቡ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ነገ ሐምሌ 24/2017 “በመትከል ማንሰራራት” በሚል መሪ ሀሳብ በሚካሔደው የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ላይ የክልሉ ህዝብ የላቀ ተሳትፎ እንዲያደርግ ጥሪ አቀረቡ፡፡
በአገር አቀፍ ደረጃ 700 ሚሊዮን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ደግሞ 6 ነጥብ 8 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀንበር መትከል የሚያስችል ዝግጅት መጠናቀቁን ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።
ይህን ሀገራዊ ጥሪ ከግብ ለማድረስ የክልሉ ህዝብ በነቂስ በመውጣት አሻራውን ማሳረፍ እንዳለበት ርዕሰ መስተዳድሩ ጥሪ ማቅረባቸውን የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመለክታል።

More Stories
በትራንስፕርት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ እየተደረገ ባለው ከታሪፍ በላይ ጭማሪ ለተለያዩ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ችግሮች እየተጋለጥን ነው ሲሉ በወልቂጤ ከተማ መናኽሪያ አግኝተን ያነጋገርናቸው ተሳፋሪዎች ተናገሩ
ወጣቱ ትዉልድ በግብርናዉ ዘርፍ ያሉ አማራጮችን ተጠቅሞ የኢኮኖሚ ባለቤት እንዲሆን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በዳውሮ ዞን ባሌ ከተማ አስተዳደር ሶዶ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን መርቀው ከፈቱ