ሀገር አቀፍ የክለቦች ሻምፒዮና ውድድር ያለምንም ችግር እንዲካሄድ በቂ ዝግጅት መደረጉን የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ ገለፁ
ዝግጅቱን አስመልክቶ መግለጫ የሰጡት የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ ኣሪ ዞን የሠላም ተምሳሌት ፤ህዝቦቿ እንግዳ ተቀባይ በመሆናቸው ወደ ዞኑ የሚመጡ የስፖርት ልዑካን ቡድን ወደ ሁለተኛ እቤታቸው እንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል ።
በአሁን ወቅት ከሀገሪቱ አራቱም ማዕዘናት የስፖርት ልዑካን ቡድን ወደ ጂንካ ከተማ እየገቡ ሲሆን መላው የአካባቢው ህዝብ እንግዶችን ተቀብለው እንዲያስተናግዱ ጥሪ አቅርበዋል።
በተለይ እንዲህ ዓይነት ውድድሮች ኢትዮጵያዊያን በመላው ሀገሪቱ ተዘዋውረው ኢትዮጵያን ለመገንዘብ ትልቅ ዕድልን ይፈጥራል ሲሉም ዋና አስተዳዳሪው ገልፀዋል።
የኣሪ ዞን ፓሊስ አዛዥ ዋና ኢንስፔክተር መሠለ ገብሬ እና የኣሪ ዞን ሠላምና ፀጥታ መምሪያ ሀላፊ አቶ ማታዶ በርቢ በጋራ እንደገለፁት ስፖርታዊ ውድድሩ ያለምንም ችግር እንዲጠናቀቅ በቂ ዝግጅት ተደርጎ የስፖርት ልዑካኑን ቅበላ እየተደረገ እንዳለ አስረድተዋል።
አጠቃላይ የፀጥታው መዋቅር ለውድድሩ ስኬት ሀላፊነቱን እንደሚወጣ የገለፁት የመንግስት የሥራ ሀላፊዎች ይህንን ከመላው የአካባቢው ህዝብ ጋር በጋራ ቅንጅት እየተሠራ ስለመሆኑም ተናግረዋል ።
የአካባቢው ነዋሪዎችም እንግዶችን ተቀብለው በማስተናገድ ውድድሩ እስኪጠናቀቅ ድረስ አስፈላጊ በሆኑ ጉዳዮች ሁሉ ከጎናቸው እንደሚቆሙ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
ሀገር አቀፍ የክለቦች ሻምፒዮና ውድድር በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በኣሪ ዞን አስተናጋጅነት ከሰኔ 28/2017 ዓ/ም ጀምሮ ለአንድ ወር ያህል እንደሚቆይ ተገልጿል ።
ኣሪ ዞን ጂንካ ከተማ በቅርቡ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የክለቦች ሻምፒዮና ውድድርን ማስተናገዱ የሚታወስ ነው።
ዘጋቢ:-ተመስገን አበራ-ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
ማንቸስተር ዩናይትድ ግብ ጠባቂ አስፈረመ
ማንቸስተር ዩናይትድ አንድሬ ሳንቶስን አስፈረመ
የ2018 የCBE የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ እና የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪሚየር ሊግ ውድድርን በማሸነፍ ሁለት ዋንጫ ላነሳው የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ክልሉ ያዘጋጀውን የዕውቅናና የሽልማት ፕሮግራም ዛሬ ሰኞ ሐምሌ 06/2018 ከቀኑ 12፡00 ጀምሮ በሀዋሳ ሀይሌ ሪዞርት ይካሄዳል።