በየደረጃው ያለው አመራር አንድነትና ወንድማማችነት በማጠናከር የሕዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ ተጠየቀ
ሀዋሳ፡ ሰኔ 09/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በየደረጃው ያለው አመራር አንድነትና ወንድማማችነት በማጠናከር የሕዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ በምክትል ርዕስ መስተዳድር ማዕረግ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተፈሪ አባተ አስገነዘቡ።
በጎፋ ዞን የገዜ ጎፋ ወረዳ እና ቡልቂ ከተማ አሰተዳደር ተወላጆች ምሁራን አንድነት እና ወንድማማችነት ማጠናከሪያ መድረክ እየተካሄደ ነው፡፡
በጎፋ ዞን የቡልቂ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጂነር ተመስገን ጣሰውና የገዜ ጎፋ ወረዳ ዋና አሰተዳደሪ አቶ አብርሃም ብርሃኑ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ባስተላለፉበት ወቅት፤ መድረኩ የአካባቢ ተወላጆች በአካባቢ ሠላም፣ ልማት እና አንድነት ላይ ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግ ያለመ መሆኑን ተናግረዋል።
አቶ ተፈሪ አባተ በምክክር መድረኩ እንዳሉት፤ በአካባቢው ተወላጆች መካከል የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት በመፍጠር ወንድማማችነትን ይበልጥ ለማጠናከር አሰፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
በየደረጃው ያለው አመራር ከመጠላለፍና ከመገፋፋት አስከፊ የፖለቲካ አዙሪት በመላቀቅ አንድነትና ወንድማማችነት በማጠናከር የሕዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ አሳስበዋል።
የቡልቂ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሀይሉ ባበና፤ በአካባቢው የተሰሩ መሠረተ ልማቶች የተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀም ዙሪያ ሰነድ አቅርበው ውይይት እየተደረገ ይገኛል።
ዘጋቢ፡ ስንታየሁ መላቱ – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ