በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማትና ኢንዱስትሪ ክላስተር አስተባባሪና የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤል የከተማ ልማት ስራዎችን ወደ ላቀ ደረጃ ማሳደግ የሚያስችል ስራ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
በተለይም በኮሪደር ልማት፣ በመሠረተ ልማት፣ በማህበር ቤት ልማት፣ በኢንዱስትሪ ዞን መሬት ማካለልና ማልማት ስራዎች ላይ የተሻለ አፈፃፀም ተመልክተናል ብለዋል።
እስካሁን ያልተጀመረው የአንድ ከተማ አንድ ፕሮጀክት ስራ በአስቸኳይ እንዲሰራ መመሪያ ሰጥተዋል፡፡
ለአቅመ ደካማ የህብረተሰብ ክፍሎች ተገንብቶ የተላለፈው የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ የሚበረታታና ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል ሲሉም ጠቁመዋል ።
በግንባታ ደረጃ የተያዘው የኮሪደር ልማት ዕቅድ አነስተኛና እንዲጠናቀቅ ከተያዘው ጊዜ አንጻር አፈጻጸሙ ዝቅተኛ በመሆኑ ፍጥነትን ይጠይቃል ብለዋል፡፡
የክላስተር ቢሮው ግንባታ ከሌሎች ሳይቶች አንጻር የተጓተተ በመሆኑ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ግብረ መልስ ተሰጥቶበታል፡፡
ዘጋቢ፤ ባዬ በልስቲ

More Stories
የቡርጂ ዞን ምክር ቤት አቶ ትንሳኤ ዮሐንስ ወጌ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አድርጎ ሾመ
የወባ በሽታ ስርጭትን የመከላከልና የመቆጣጠርን ጉዳይ ቀዳሚ ተግባር አድርጎ እየሰራ መሆኑን የስልጤ ዞን ጤና መምሪያ አስታወቀ
አገልግሎት አሰጣጡን በማዘመን ተገልጋዩን ለማርካት እየሰራ መሆኑን የአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል አስታወቀ