በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማትና ኢንዱስትሪ ክላስተር አስተባባሪና የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤል የከተማ ልማት ስራዎችን ወደ ላቀ ደረጃ ማሳደግ የሚያስችል ስራ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
በተለይም በኮሪደር ልማት፣ በመሠረተ ልማት፣ በማህበር ቤት ልማት፣ በኢንዱስትሪ ዞን መሬት ማካለልና ማልማት ስራዎች ላይ የተሻለ አፈፃፀም ተመልክተናል ብለዋል።
እስካሁን ያልተጀመረው የአንድ ከተማ አንድ ፕሮጀክት ስራ በአስቸኳይ እንዲሰራ መመሪያ ሰጥተዋል፡፡
ለአቅመ ደካማ የህብረተሰብ ክፍሎች ተገንብቶ የተላለፈው የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ የሚበረታታና ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል ሲሉም ጠቁመዋል ።
በግንባታ ደረጃ የተያዘው የኮሪደር ልማት ዕቅድ አነስተኛና እንዲጠናቀቅ ከተያዘው ጊዜ አንጻር አፈጻጸሙ ዝቅተኛ በመሆኑ ፍጥነትን ይጠይቃል ብለዋል፡፡
የክላስተር ቢሮው ግንባታ ከሌሎች ሳይቶች አንጻር የተጓተተ በመሆኑ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ግብረ መልስ ተሰጥቶበታል፡፡
ዘጋቢ፤ ባዬ በልስቲ

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ