በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማትና ኢንዱስትሪ ክላስተር አስተባባሪና የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤል የከተማ ልማት ስራዎችን ወደ ላቀ ደረጃ ማሳደግ የሚያስችል ስራ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
በተለይም በኮሪደር ልማት፣ በመሠረተ ልማት፣ በማህበር ቤት ልማት፣ በኢንዱስትሪ ዞን መሬት ማካለልና ማልማት ስራዎች ላይ የተሻለ አፈፃፀም ተመልክተናል ብለዋል።
እስካሁን ያልተጀመረው የአንድ ከተማ አንድ ፕሮጀክት ስራ በአስቸኳይ እንዲሰራ መመሪያ ሰጥተዋል፡፡
ለአቅመ ደካማ የህብረተሰብ ክፍሎች ተገንብቶ የተላለፈው የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ የሚበረታታና ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል ሲሉም ጠቁመዋል ።
በግንባታ ደረጃ የተያዘው የኮሪደር ልማት ዕቅድ አነስተኛና እንዲጠናቀቅ ከተያዘው ጊዜ አንጻር አፈጻጸሙ ዝቅተኛ በመሆኑ ፍጥነትን ይጠይቃል ብለዋል፡፡
የክላስተር ቢሮው ግንባታ ከሌሎች ሳይቶች አንጻር የተጓተተ በመሆኑ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ግብረ መልስ ተሰጥቶበታል፡፡
ዘጋቢ፤ ባዬ በልስቲ

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ