ተወዳዳሪ ዜጋ እንድትሆኑ ሳትሰርቁ ጠንክራችሁ ፈተናችሁን በራሳችሁ ሥሩ – ብርሀኑ ነጋ (ፕ/ር)
የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ብርሀኑ ነጋ (ፕ/ር) በከምባታ ዞን ሺንሺቾ አጠቃላይ ከፍተኛ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተገኝተው የ6ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና መርሐ ግብርን አስጀምረዋል።
በመርሐ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ ጨምሮ ሌሎች የሥራ ኃላፊዎችም ተገኝተዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሀኑ ነጋ (ፕ/ር) በዚሁ ወቅት፤ ከስርቆት እና ከማጭበርበር በጸዳ መልኩ ጠንክራችሁ ፈተናችሁን ሥሩ በማለት ለተማሪዎች መልዕክት አስተላልፈዋል።
ተማሪዎች በራሳቸው የመተማመን አቅማቸውን በማሳደግ ተወዳዳሪ ዜጋ ሆነው በሀገሪቱ እድገት ላይ አሻራቸውን ማሳረፍ እንዲችሉም ሚኒስትሩ አበረታተዋል።
በተጨማሪም ሚኒስትሩ በሺንሺቾ ከተማ በብራይት ቪዥን ቅድመ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ለህጻናት እየተሰጠ ያለውን ትምህርት ምልከታ አድርገዋል።
አቶ አንተነህ ፈቃዱ በበኩላቸው በክልሉ ለመጀመሪያ ጊዜ በሚሰጠው የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና 98 ሺህ 107 ተማሪዎች ፈተናውን እንደሚወስዱ ተናግረዋል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ የትምህርት ፖሊሲ ለውጥ መደረጉን ተከትሎ የምዘና ስርዓት በመቀየሩ የተማሪዎችን ክህሎት በማሳደግ ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖረውም አብራርተዋል።
ዘጋቢ ፡ ወንደሰን ሽመልስ

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ