በየም ብሔረሰብ የባህላዊ መድኃኒት ለቀማና ቅመማ ጥናት ውጤት ላይ ያተኮረ የግምገማ መድረክ በሳጃ ከተማ እየተካሄደ ነው
በየም ብሔረሰብ የባህላዊ መድኃኒት ለቀማና ቅመማ ጥናት ውጤት ላይ ያተኮረ የግምገማ መድረክ “ሀገር በቀል ዕውቀቶች እና ባህላዊ እሴቶች ለሁለንተናዊ ብልጽግና” በሚል መሪ ቃል በሳጃ ከተማ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል።
የግምገማ መድረኩ የኢፌዲሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ስለመሆኑም ተመላክቷል።
በመድረኩ ላይ የኢፌዲሪ ባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ነፊሳ አብዱልማዲ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብሄረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ እና የየም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሽመልስ እጅጉን ጨምሮ የክልል እና የዞን ክፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ማሙዬ ፊጣ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
የህፃናት የወደፊት የኑሮ ሁኔታ እንዲሻሻልና የተሻለ ሀገር ተረካቢ ትውልድ ለመገንባት እየሠራ እንደሚገኝ የጉራጌ ህዝብ ራስ አገዝ ልማት ድርጅት ገለፀ
5ኛው አገራዊ የሠላም ኮንፈረንስን በተመለከተ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት የኮሙኒኬሽን አገልግሎት የተላለፈ መልዕክት
ፈጣን ፣ ወቅታዊ እና ተአማኒ መረጃን ተደራሽ ለማድረግ ዘመኑን የሚመጥን አሰራርን መዘርጋት እንደሚገባ ተገለጸ