በየም ብሔረሰብ የባህላዊ መድኃኒት ለቀማና ቅመማ ጥናት ውጤት ላይ ያተኮረ የግምገማ መድረክ በሳጃ ከተማ እየተካሄደ ነው
በየም ብሔረሰብ የባህላዊ መድኃኒት ለቀማና ቅመማ ጥናት ውጤት ላይ ያተኮረ የግምገማ መድረክ “ሀገር በቀል ዕውቀቶች እና ባህላዊ እሴቶች ለሁለንተናዊ ብልጽግና” በሚል መሪ ቃል በሳጃ ከተማ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል።
የግምገማ መድረኩ የኢፌዲሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ስለመሆኑም ተመላክቷል።
በመድረኩ ላይ የኢፌዲሪ ባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ነፊሳ አብዱልማዲ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብሄረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ እና የየም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሽመልስ እጅጉን ጨምሮ የክልል እና የዞን ክፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ማሙዬ ፊጣ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ