በየም ብሔረሰብ የባህላዊ መድኃኒት ለቀማና ቅመማ ጥናት ውጤት ላይ ያተኮረ የግምገማ መድረክ በሳጃ ከተማ እየተካሄደ ነው
በየም ብሔረሰብ የባህላዊ መድኃኒት ለቀማና ቅመማ ጥናት ውጤት ላይ ያተኮረ የግምገማ መድረክ “ሀገር በቀል ዕውቀቶች እና ባህላዊ እሴቶች ለሁለንተናዊ ብልጽግና” በሚል መሪ ቃል በሳጃ ከተማ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል።
የግምገማ መድረኩ የኢፌዲሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ስለመሆኑም ተመላክቷል።
በመድረኩ ላይ የኢፌዲሪ ባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ነፊሳ አብዱልማዲ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብሄረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ እና የየም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሽመልስ እጅጉን ጨምሮ የክልል እና የዞን ክፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ማሙዬ ፊጣ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ
ሁሉም ሰው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በቀጣይ የሚያስተዳድረውን መንግስት መምረጥ እንዲችል የምርጫ ካርድ በወቅቱ መያዝ እንደሚጠበቅበት ተገለጸ