በየም ብሔረሰብ የባህላዊ መድኃኒት ለቀማና ቅመማ ጥናት ውጤት ላይ ያተኮረ የግምገማ መድረክ በሳጃ ከተማ እየተካሄደ ነው
በየም ብሔረሰብ የባህላዊ መድኃኒት ለቀማና ቅመማ ጥናት ውጤት ላይ ያተኮረ የግምገማ መድረክ “ሀገር በቀል ዕውቀቶች እና ባህላዊ እሴቶች ለሁለንተናዊ ብልጽግና” በሚል መሪ ቃል በሳጃ ከተማ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል።
የግምገማ መድረኩ የኢፌዲሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ስለመሆኑም ተመላክቷል።
በመድረኩ ላይ የኢፌዲሪ ባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ነፊሳ አብዱልማዲ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብሄረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ እና የየም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሽመልስ እጅጉን ጨምሮ የክልል እና የዞን ክፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ማሙዬ ፊጣ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል