የወረዳው የስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ብሩክ በላይነህ በወረዳው ለሶስተኛ ዙር በማህበር ለተደራጁ ስራ ፈላጊ ወጣቶች ኮርማ፣ በግና ፍየል፣ ቅቤ እንዲሁም እህል ከ3 ሚሊዮን 300 ሺህ ብር በላይ በሆነ ወጭ ግዢ በመፈጸም ስርጭት ተደርጓል ነው ያሉት ፡፡
የስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ጽ/ቤት ምክትልና የገጠር ስራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ ኃላፊ ወይዘሮ ገነት ኃ/ማርያም በበኩላቸው፤ በተያዘው በጀት ዓመት በ5 ቀበሌ ለ462 ወጣቶች የስራ ዕድል ለመፍጠር ግብ ተጥሎ በዚህም ከዕቅዱ አንጻር መቶ በመቶ ማሳካት መቻሉንም አስረድተዋል።
ለወጣቶች ተጨማሪ ድጋፍ ፕሮጀክት በህይወት ክህሎት ስልጠና እና በስብዕና ግንባታ እንዲሁም ኮርማ፣ በግና ፍየል፣ ቅቤ፣ ዶሮ እና እህል ግዢ በመፈጸም ለኢንተርፕራይዞች በማቅረብ አብረው እየሰሩ እንዳሉ የተናገሩት ወይዘሮ ገነት ከ3 ሚሊዮን 300 ሺህ ብር በላይ በሆነ ወጭ በዚህ ፕሮጀክት ታቅፈው ለሚገኙ 5 ቀበሌዎች ለ33 ኢንተርፕራይዞች ግዢ ፈጽሞ ስርጭት እያደረገ እንደሚገኝም ገልጿል።
በቦታው አግኝተን ካነጋገርናቸው ተጠቃሚ ወጣቶች መካከል በዛብሽ ባንጫ፣ ታገሰ ጎዳንች እና ጌታሁን አይናቶ በሰጡት አስተያየትም የአደይ ፕሮጀክት ከወረዳው ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ጽ/ቤት ጋር በመሆን የተለያዩ የክህሎት ስልጠናና ኮርማ፣ በግና ፍየል፣ ቅቤ፣ ዶሮ እና እህል ግዢ በመፈጸም ስርጭት እያደረገላቸው እንደሚገኝ ተናግረዋል።
ወጣቶች ከስራ ጠባቂነት ወደ ስራ ፈጣሪነት በመሸጋገራቸው ኑሯቸውን ለማሻሻል የተሻለ ዕድል እንደሰጣቸው ተናግረዋል።
ዘጋቢ ፡ አንዱአለም ኡማ – ከዋካ ቅርንጫፍ

More Stories
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) መጭው ጊዜ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ብርሃን የምንሸጋገርበት ብሩህ ዘመን መሆኑን ተናገሩ
በተቀሩት አጭር ቀናት ህብረተሠቡ የመራጭነት ካርዱን በመውሰድ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳና አካባቢው የፌደራልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጥሪ አቀረቡ