የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት የ10 ወራት አፈጻጸም እና የቀጣይ የክረምት ወራት ቅድመ ዝግጅት ግምገማ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ እያካሄደ ይገኛል

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት የ10 ወራት አፈጻጸም እና የቀጣይ የክረምት ወራት ቅድመ ዝግጅት ግምገማ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ እያካሄደ ይገኛል

በ2020 – 30 የወባ ወረርሽኝን ለመከላከል በክልሉ እየተሰራ መሆኑን ምክትል ቢሮ ኃላፊና የጤና ፕሮግራሞች ዘርፍ ኃላፊ አቶ አሸናፊ ጰጥሮስ በመክፈቻ ንግግራቸው ገልፀዋል፡፡

በ2016 በጀት ዓመት የተከሰተው የወባ ወረርሸኝ ከፍተኛ ጉዳት ሳያደርስ መከላከልና መቆጣጠር መቻሉንም ተናግረዋል፡፡

በቀጣይም ወባን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ውሃ ያቆሩ ቦታዎችን የማፋሰስና የማዳፈን ሰራ ህዝብን ባሳተፈ መልኩ እንደሚሰራም ተጠቁሟል፡፡

ዘጋቢ፡ አበባ ሌንዲዶ