የጠምባሮ ልማት ማህበር የሀዋሳ ዙሪያ ማስተባበሪያ በይፋ ተመሰረተ
ልማት ማህበሩ ግንቦት 9 ቀን 2016 ዓ.ም በይፋ ከተመሰረተ በኋላ አዲስ አበባና ሀደሮ ከተማ ቅርንጫፎች በመክፈት ስራዎች እየሰራ ነው።
ከኢፌድሪ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ወስዶ ስራውን የጀመረው የጠምባሮ ልማት ማህበር የተለያዩ የልማት ስራዎችን ለመስራት ዓላማ ይዞ በአዋጅ የተቋቋመ ነው።
ማህበሩ በትምርት፣ በጤና፣ በመሰረተ ልማት፣ በግብርናና አካባቢ ጥበቃ አንዲሁም በስራ ዕድል ፈጠራ ስራዎችን ለመስራት እንቅስቃሴ ጀምሯል።
ዛሬ ላይም በሀዋሳና አካባቢው ከሚኖሩ የብሄረሰቡ ተወላጆች ጋር በቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ በሀዋሳ ከተማ ውይይት ተደርጓል።
ዘጋቢ፡- ባዬ በልስቲ

More Stories
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ
በከተማው በተያዘው በጀት ዓመት በ5 ወራት ውስጥ 1 ቢሊየን 5 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ
የሰራተኞች የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበር ብዙዎችን የቤት ባለቤት ማድረጉ ተገለጸ