የጠምባሮ ልማት ማህበር የሀዋሳ ዙሪያ ማስተባበሪያ በይፋ ተመሰረተ
ልማት ማህበሩ ግንቦት 9 ቀን 2016 ዓ.ም በይፋ ከተመሰረተ በኋላ አዲስ አበባና ሀደሮ ከተማ ቅርንጫፎች በመክፈት ስራዎች እየሰራ ነው።
ከኢፌድሪ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ወስዶ ስራውን የጀመረው የጠምባሮ ልማት ማህበር የተለያዩ የልማት ስራዎችን ለመስራት ዓላማ ይዞ በአዋጅ የተቋቋመ ነው።
ማህበሩ በትምርት፣ በጤና፣ በመሰረተ ልማት፣ በግብርናና አካባቢ ጥበቃ አንዲሁም በስራ ዕድል ፈጠራ ስራዎችን ለመስራት እንቅስቃሴ ጀምሯል።
ዛሬ ላይም በሀዋሳና አካባቢው ከሚኖሩ የብሄረሰቡ ተወላጆች ጋር በቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ በሀዋሳ ከተማ ውይይት ተደርጓል።
ዘጋቢ፡- ባዬ በልስቲ

More Stories
የጤና ፕሮግራምና ኤች አይ ቪ መከላከልና መቆጣጠር ዘርፍ የተግባር አፈፃፀም ግምገማና የውይይት መድረክ ተካሄደ
ወጣቶች ግጭትን በመከላከል ረገድ ሊኖራቸው የሚገባ ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ
ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ በመመዝገብ የሚፈልገውን የፖለቲካ ፓርቲ እንዲመርጥ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) ጥሪ አቀረበ