የጠምባሮ ልማት ማህበር የሀዋሳ ዙሪያ ማስተባበሪያ በይፋ ተመሰረተ
ልማት ማህበሩ ግንቦት 9 ቀን 2016 ዓ.ም በይፋ ከተመሰረተ በኋላ አዲስ አበባና ሀደሮ ከተማ ቅርንጫፎች በመክፈት ስራዎች እየሰራ ነው።
ከኢፌድሪ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ወስዶ ስራውን የጀመረው የጠምባሮ ልማት ማህበር የተለያዩ የልማት ስራዎችን ለመስራት ዓላማ ይዞ በአዋጅ የተቋቋመ ነው።
ማህበሩ በትምርት፣ በጤና፣ በመሰረተ ልማት፣ በግብርናና አካባቢ ጥበቃ አንዲሁም በስራ ዕድል ፈጠራ ስራዎችን ለመስራት እንቅስቃሴ ጀምሯል።
ዛሬ ላይም በሀዋሳና አካባቢው ከሚኖሩ የብሄረሰቡ ተወላጆች ጋር በቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ በሀዋሳ ከተማ ውይይት ተደርጓል።
ዘጋቢ፡- ባዬ በልስቲ

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል