በጉራጌ ዞን እኖር ኤነር መገር ወረዳ የተለያዩ የመሠረተ ልማቶች የምረቃ ስነ-ስርዓት እየተካሄደ ይገኛል
በወረዳው የምረቃ ስነ-ስርዓት እየተከናወነባቸው ከሚገኙ መሠረተ ልማቶች መካከል የወረዳው አስተዳደር ባለአራት ወለል ህንፃ እና የወረዳው ፍርድ ቤት ህንፃ ይገኙበታል።
የእኖር ኤነር መገር ወረዳ አስተዳደር ከ104 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ አድርጎ ያስገነባቸው ፕሮጀክቶችን አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት በማድረግ ላይ ይገኛል።
በተጨማሪም በወረዳው የገጠር ኮሪደር ልማት እንቅስቃሴ የደረሰበት ደረጃ የመስክ ምልከታ ተደርጓል።
በስነ-ስርዓቱ ላይ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ፣ የዞኑ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አለማየሁ ገ/መስቀልን ጨምሮ በየደረጃው የሚገኙ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳ እና ከተማ አስተዳደር የስራ ኃላፊዎች፣ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ጥሪ የተደረገላቸው የአካባቢው ተወላጆችና ባለሀብቶች እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዎች በመታደም ላይ ናቸው።
ዘጋቢ፡ ሪድዋን ሰፋ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል