በጉራጌ ዞን እኖር ኤነር መገር ወረዳ የተለያዩ የመሠረተ ልማቶች የምረቃ ስነ-ስርዓት እየተካሄደ ይገኛል
በወረዳው የምረቃ ስነ-ስርዓት እየተከናወነባቸው ከሚገኙ መሠረተ ልማቶች መካከል የወረዳው አስተዳደር ባለአራት ወለል ህንፃ እና የወረዳው ፍርድ ቤት ህንፃ ይገኙበታል።
የእኖር ኤነር መገር ወረዳ አስተዳደር ከ104 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ አድርጎ ያስገነባቸው ፕሮጀክቶችን አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት በማድረግ ላይ ይገኛል።
በተጨማሪም በወረዳው የገጠር ኮሪደር ልማት እንቅስቃሴ የደረሰበት ደረጃ የመስክ ምልከታ ተደርጓል።
በስነ-ስርዓቱ ላይ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ፣ የዞኑ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አለማየሁ ገ/መስቀልን ጨምሮ በየደረጃው የሚገኙ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳ እና ከተማ አስተዳደር የስራ ኃላፊዎች፣ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ጥሪ የተደረገላቸው የአካባቢው ተወላጆችና ባለሀብቶች እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዎች በመታደም ላይ ናቸው።
ዘጋቢ፡ ሪድዋን ሰፋ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ