በጉራጌ ዞን እኖር ኤነር መገር ወረዳ የተለያዩ የመሠረተ ልማቶች የምረቃ ስነ-ስርዓት እየተካሄደ ይገኛል
በወረዳው የምረቃ ስነ-ስርዓት እየተከናወነባቸው ከሚገኙ መሠረተ ልማቶች መካከል የወረዳው አስተዳደር ባለአራት ወለል ህንፃ እና የወረዳው ፍርድ ቤት ህንፃ ይገኙበታል።
የእኖር ኤነር መገር ወረዳ አስተዳደር ከ104 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ አድርጎ ያስገነባቸው ፕሮጀክቶችን አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት በማድረግ ላይ ይገኛል።
በተጨማሪም በወረዳው የገጠር ኮሪደር ልማት እንቅስቃሴ የደረሰበት ደረጃ የመስክ ምልከታ ተደርጓል።
በስነ-ስርዓቱ ላይ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ፣ የዞኑ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አለማየሁ ገ/መስቀልን ጨምሮ በየደረጃው የሚገኙ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳ እና ከተማ አስተዳደር የስራ ኃላፊዎች፣ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ጥሪ የተደረገላቸው የአካባቢው ተወላጆችና ባለሀብቶች እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዎች በመታደም ላይ ናቸው።
ዘጋቢ፡ ሪድዋን ሰፋ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ