ወንጀልን የመከላከል መርህን መሠረት በማድረግ የሕብረተሰቡን ሠላምና ደህንነት ማስጠበቅ ይገባል – የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ
ወንጀልን የመከላከል መርህን መሠረት በማድረግ የሕብረተሰቡን ሠላምና ደህንነት ለማስጠበቅ የሚሊሻ አባላት ከፀጥታ አካላት ጋር ሊሠሩ እንደሚገባ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ገለፁ።
“በጀግነት መጠበቅ በሰብዓዊነት ማገልገል” በሚል መሪ ቃል በዞኑ የሐመር ወረዳ ሚሊሻ ጽህፈት ቤት 2 መቶ 59 የሚሊሻ አባላትን አሰልጥኖ አስመርቋል።
በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ተገኝተው መልክት ያስተላለፉት የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ፤ ወንጀልን የመከላከል መርህን በመከተል የሕብረተሰቡን ሠላምና ደህንነት ለማስጠበቅ ተመራቂ ሚሊሻ አባላት ከፀጥታ አካላት ጋር በቅንጅት እንዲሠሩ አሳስበዋል።
የደቡብ ኦሞ ዞን ሠላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ጎላ ጎዳቦ በበኩላቸው፤ ተመራቂዎቹ የማህበረሰቡንና የአካባቢውን ዘላቂ ሠላም ለማስጠበቅ ከመንግሥት ጎን በመቆም ወንጀል የመከላከል ሥራውን በኃላፊነት እንዲወጡ የሥራ መመሪያም ሰጥተዋል።
የሐመር ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሣሙኤል ጋርሾ እንደገለፁት፤ የእድገትና የብልፅግና ዕቅዶችን ለማሳካትና የአርብቶ አደሩን ማህበረሰብ ዘላቂ ሠላምና ልማትን ለማረጋገጥ የሚሊሻ አባላት ምረቃ ተጨማሪ አቅም መፍጠሩን አስረድተዋል።
የሐመር ወረዳ ሠላምና ፀጥታ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኡቲና አሪ እና አሰልጣኝ ኮንስታብል ቢንያም ዴሬ በጋራ እንደገለፁት፤ ከ34 ቀበሌያት የተውጣጡ 2 መቶ 59 የሚሊሻ አባላት መሠረታዊ የውትድርና ዕውቀትና ክህሎት ስልጠና አግኝተው ለምረቃ በቅተዋል።
ከሕብረተሰቡና ከፀጥታ አካላት ጋር በመሆን አካባቢያቸውን በተሻለ ደረጃ መጠበቅ የሚያስችል ዕውቀት ማግኘታቸውን ሰልጣኝ ምሩቃን ተናግረዋል።
ስልጠናው በስኬት እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላትና ሰልጣኞች የምስጋናና የዕውቅና ሰርተፊኬት ተሰጥቷቸዋል።
ዘጋቢ፡ ተመስገን አሰፋ – ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
የኢፌዲሪ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ከ82 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ መቆርቆር ቀበሌ ያስገነባው የንጹህ መጠ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
የኡዱሂያ የዕርድ ስርዓት….የአብሮነት ነፀብራቅ
በቅርቡ በሚሰጠው የ6ኛ እና የ8ኛ ክልላዊ ፈተና ላይ ከ53 ሺህ በላይ ተማሪዎች ለፈተና እንደሚቀርቡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀዲያ ዞን ትምህርት መመሪያ አስታወቀ