ሚዲያን ለአዎንታዊ ነገር በመጠቀም ወጣቱ ሀገርን መገንባት አለበት – የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን
ሀዋሳ፡ ነሐሴ 09/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) ሚዲያን ለአዎንታዊ ነገር በመጠቀም ወጣቱ ሀገርን መገንባት አለበት ሲል የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን አስታወቀ፡፡
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዲላ ከተማ ከ1 መቶ 50 በላይ ለሚሆኑ የሚዲያ ባለሙያዎችና ወጣቶች ስልጠና እየሰጠ ነው።
በስልጠናው ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ(ዶ/ር) እንደተናገሩት፤ በዲጂታል ዓለም ውስጥ ሚዲያ ያለው ተጽዕኖ የጎላ ነው።
ሚዲያን ለሀገር ግንባታ የተጠቀሙ ሀገራት ሀገራቸውን እየገነቡ ናቸው ያሉት አስተዳዳሪው፤ ይህን የሚደግፉ ወጣቶችን ማፍራት አስፈላጊ ነው ብለዋል።
እሴቶቻችንን ሊሸረሽሩ የሚችሉ መረጃዎችን ወጣቶች በጋራ መከላከልና በአቅም ግንባታው ዘርፍ የተጀመሩ ተግባራትም መጠናከር እንዳለባቸው አሳስበዋል።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ምስራቅ ጌቱ እንደገለጹት፤ ስልጠናው የሚዲያና የዲጂታል መረጃ አጠቃቀም ክህሎትን ለማሳደግ፣ የተሳሳተ መረጃን ለማጣራት እና ማህበራዊ ሚዲያን ለልማትና ለአገር ግንባታ ለመጠቀም የሚያግዝ ነው።
ባለስልጣኑ በተሰጠው ስልጣን የአቅም ግንባታ ላይ እየሠራ ነው ብለው፤ ሚዲያን ለአዎንታዊ ነገር በመጠቀም ወጣቱ ሀገር መገንባት እንዳለበት አሳስበዋል።
ባለስልጣኑ ከስልጠናው ጎን ለጎን በተለያዩ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎቶች ድጋፍ የሚያደርግ ይሆናልም ተብሏል።
ከመገናኛ ብዙሃን ባለስልጣኑ ፈቃድ ያገኙ 3 መቶ 29 ሚዲያዎችንና ከ2 ሺህ 5 መቶ በላይ የማስታወቂያ ድርጅቶችንና ሌሎችንም የሚያስተዳድር ተቋም መሆኑ ተመላክቷል።
ዘጋቢ: እስራኤል ቅጣው – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
በ2018 በጀት ዓመት የተቀመጡ ግቦችን በማሳካት የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ተችሏል – አቶ ፍቅሬ አማን
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎትና ከኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሚስዮኖች ጋር በመተባበር በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው 12 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አበረከተ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው