በጉራጌ ዞን ጌታ ወረዳ የተለያዩ የመሠረተ ልማት ስራዎች የምረቃ ስነ-ስርዓት እየተካሄደ ይገኛል
በወረዳው የምረቃ ስነ-ስርዓት እየተካሄደባቸው ከሚገኙ መሠረተ ልማት ስራዎች መካከል የመንገድ መሰረተ ልማት፣ የወረዳው ጤና ጽህፈት ቤት ግንባታ እና የቋንጤ የማህበረሰብ መድኃት ቤት እንዲሁም ከ100 ሚሊየን ብር በላይ የሚፈጀው ጌታ ወረዳ የባህል አዳራሽ ግንባታ መሰረተ ድንጋይ የማኖር ስነ-ስርዓት በመርሃ ግብሩ መሰረት እየተካሄደ ይገኛል።
በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ፣ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አለማየሁ ገ/መስቀልን ጨምሮ የክልልና የዞን የስራ ሀላፊዎች፣ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ጥሪ የተደረገላቸው የአካባቢ ተወላጆችና ባለሀብቶች እዲሁም የአካባቢ ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ተዘራ በቀለ – ከወልቂጤ ጣቢያችን
More Stories
የኢፌዲሪ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ከ82 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ መቆርቆር ቀበሌ ያስገነባው የንጹህ መጠ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
የኡዱሂያ የዕርድ ስርዓት….የአብሮነት ነፀብራቅ
በቅርቡ በሚሰጠው የ6ኛ እና የ8ኛ ክልላዊ ፈተና ላይ ከ53 ሺህ በላይ ተማሪዎች ለፈተና እንደሚቀርቡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀዲያ ዞን ትምህርት መመሪያ አስታወቀ