በጉራጌ ዞን ጌታ ወረዳ የተለያዩ የመሠረተ ልማት ስራዎች የምረቃ ስነ-ስርዓት እየተካሄደ ይገኛል
በወረዳው የምረቃ ስነ-ስርዓት እየተካሄደባቸው ከሚገኙ መሠረተ ልማት ስራዎች መካከል የመንገድ መሰረተ ልማት፣ የወረዳው ጤና ጽህፈት ቤት ግንባታ እና የቋንጤ የማህበረሰብ መድኃት ቤት እንዲሁም ከ100 ሚሊየን ብር በላይ የሚፈጀው ጌታ ወረዳ የባህል አዳራሽ ግንባታ መሰረተ ድንጋይ የማኖር ስነ-ስርዓት በመርሃ ግብሩ መሰረት እየተካሄደ ይገኛል።
በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ፣ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አለማየሁ ገ/መስቀልን ጨምሮ የክልልና የዞን የስራ ሀላፊዎች፣ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ጥሪ የተደረገላቸው የአካባቢ ተወላጆችና ባለሀብቶች እዲሁም የአካባቢ ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ተዘራ በቀለ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ
ሁሉም ሰው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በቀጣይ የሚያስተዳድረውን መንግስት መምረጥ እንዲችል የምርጫ ካርድ በወቅቱ መያዝ እንደሚጠበቅበት ተገለጸ