በጉራጌ ዞን ጌታ ወረዳ የተለያዩ የመሠረተ ልማት ስራዎች የምረቃ ስነ-ስርዓት እየተካሄደ ይገኛል
በወረዳው የምረቃ ስነ-ስርዓት እየተካሄደባቸው ከሚገኙ መሠረተ ልማት ስራዎች መካከል የመንገድ መሰረተ ልማት፣ የወረዳው ጤና ጽህፈት ቤት ግንባታ እና የቋንጤ የማህበረሰብ መድኃት ቤት እንዲሁም ከ100 ሚሊየን ብር በላይ የሚፈጀው ጌታ ወረዳ የባህል አዳራሽ ግንባታ መሰረተ ድንጋይ የማኖር ስነ-ስርዓት በመርሃ ግብሩ መሰረት እየተካሄደ ይገኛል።
በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ፣ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አለማየሁ ገ/መስቀልን ጨምሮ የክልልና የዞን የስራ ሀላፊዎች፣ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ጥሪ የተደረገላቸው የአካባቢ ተወላጆችና ባለሀብቶች እዲሁም የአካባቢ ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ተዘራ በቀለ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ