በጉራጌ ዞን ጌታ ወረዳ የተለያዩ የመሠረተ ልማት ስራዎች የምረቃ ስነ-ስርዓት እየተካሄደ ይገኛል
በወረዳው የምረቃ ስነ-ስርዓት እየተካሄደባቸው ከሚገኙ መሠረተ ልማት ስራዎች መካከል የመንገድ መሰረተ ልማት፣ የወረዳው ጤና ጽህፈት ቤት ግንባታ እና የቋንጤ የማህበረሰብ መድኃት ቤት እንዲሁም ከ100 ሚሊየን ብር በላይ የሚፈጀው ጌታ ወረዳ የባህል አዳራሽ ግንባታ መሰረተ ድንጋይ የማኖር ስነ-ስርዓት በመርሃ ግብሩ መሰረት እየተካሄደ ይገኛል።
በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ፣ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አለማየሁ ገ/መስቀልን ጨምሮ የክልልና የዞን የስራ ሀላፊዎች፣ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ጥሪ የተደረገላቸው የአካባቢ ተወላጆችና ባለሀብቶች እዲሁም የአካባቢ ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ተዘራ በቀለ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
የሰራተኞች የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበር ብዙዎችን የቤት ባለቤት ማድረጉ ተገለጸ
በሁሉም ዘርፎች እንደሀገር አመርቂ ውጤቶች እየተዘመገቡ ነው – የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርዓትን በማዘመን የመረጃ ታማኝነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ