በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቀቤና ልዩ ወረዳ ሁለተኛ ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ በዛሬዉ እለት መሰጠት ተጀምሯል።
በልዩ ወረዳዉ ከ17 ሺህ በላይ ህጻናት ክትባቱን እንደሚወስዱ የቀቤና ልዩ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ገልጿል።
በልዩ ወረዳዉ ከዛሬ ግንቦት 22 ጀምሮ ለተከታታይ አራት ቀናት ቤት ለቤት ለሚሰጠዉ የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ የክልሉ ጤና ቢሮ ሀላፊዎችን ጨምሮ በየደረጃዉ የሚገኙ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ነዉ የተጀመረዉ።
ከፖሊዮ ክትባት ጎንለጎን የላንቃ መሰንጠቅ፣ ቆልማም እግር ልየታ ፣የፌስቱላ ህመም ተጠቂ ልየታ እና ሌሎችም የጤና ነክ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ተደርጎ ይሰራልም ተብሏል።
በልዩ ወረዳዉ በመጀመሪያ ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ከ13 ሺህ በላይ ህጻናት መከተባቸዉ ሲታወስ በሁለተኛዉ ዙር ከ17 ሺህ በላይ ህጻናት የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ይሆናሉ።
ዘጋቢ፡- ሪያድ ሙህዲን
More Stories
የኢፌዲሪ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ከ82 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ መቆርቆር ቀበሌ ያስገነባው የንጹህ መጠ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
የኡዱሂያ የዕርድ ስርዓት….የአብሮነት ነፀብራቅ
በቅርቡ በሚሰጠው የ6ኛ እና የ8ኛ ክልላዊ ፈተና ላይ ከ53 ሺህ በላይ ተማሪዎች ለፈተና እንደሚቀርቡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀዲያ ዞን ትምህርት መመሪያ አስታወቀ