በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቀቤና ልዩ ወረዳ ሁለተኛ ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ በዛሬዉ እለት መሰጠት ተጀምሯል።
በልዩ ወረዳዉ ከ17 ሺህ በላይ ህጻናት ክትባቱን እንደሚወስዱ የቀቤና ልዩ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ገልጿል።
በልዩ ወረዳዉ ከዛሬ ግንቦት 22 ጀምሮ ለተከታታይ አራት ቀናት ቤት ለቤት ለሚሰጠዉ የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ የክልሉ ጤና ቢሮ ሀላፊዎችን ጨምሮ በየደረጃዉ የሚገኙ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ነዉ የተጀመረዉ።
ከፖሊዮ ክትባት ጎንለጎን የላንቃ መሰንጠቅ፣ ቆልማም እግር ልየታ ፣የፌስቱላ ህመም ተጠቂ ልየታ እና ሌሎችም የጤና ነክ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ተደርጎ ይሰራልም ተብሏል።
በልዩ ወረዳዉ በመጀመሪያ ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ከ13 ሺህ በላይ ህጻናት መከተባቸዉ ሲታወስ በሁለተኛዉ ዙር ከ17 ሺህ በላይ ህጻናት የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ይሆናሉ።
ዘጋቢ፡- ሪያድ ሙህዲን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል