በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቀቤና ልዩ ወረዳ ሁለተኛ ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ በዛሬዉ እለት መሰጠት ተጀምሯል።
በልዩ ወረዳዉ ከ17 ሺህ በላይ ህጻናት ክትባቱን እንደሚወስዱ የቀቤና ልዩ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ገልጿል።
በልዩ ወረዳዉ ከዛሬ ግንቦት 22 ጀምሮ ለተከታታይ አራት ቀናት ቤት ለቤት ለሚሰጠዉ የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ የክልሉ ጤና ቢሮ ሀላፊዎችን ጨምሮ በየደረጃዉ የሚገኙ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ነዉ የተጀመረዉ።
ከፖሊዮ ክትባት ጎንለጎን የላንቃ መሰንጠቅ፣ ቆልማም እግር ልየታ ፣የፌስቱላ ህመም ተጠቂ ልየታ እና ሌሎችም የጤና ነክ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ተደርጎ ይሰራልም ተብሏል።
በልዩ ወረዳዉ በመጀመሪያ ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ከ13 ሺህ በላይ ህጻናት መከተባቸዉ ሲታወስ በሁለተኛዉ ዙር ከ17 ሺህ በላይ ህጻናት የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ይሆናሉ።
ዘጋቢ፡- ሪያድ ሙህዲን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ