ሀገራችን በአህጉርም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ የምትታወቅባቸው በርካታ እሴቶች ቀጣይነት እንዲኖራቸው የአሁኑ ትውልድ ሀላፊነት እንዳለበት የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አስገነዘበ

ሀገራችን በአህጉርም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ የምትታወቅባቸው በርካታ እሴቶች ቀጣይነት እንዲኖራቸው የአሁኑ ትውልድ ሀላፊነት እንዳለበት የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አስገነዘበ

ዩኒቨርሲቲው የሀገር በቀል ቋንቋና ባህልን ለማጎልበት ያለመ ስልጠና ለሚዲያ ባለሙያዎች እየሰጠ ይገኛል።

ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ሀብቴ ዱላ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ በአህጉርም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ የምትታወቅባቸው የበርካታ እሴቶች ባለቤት ናት ብለዋል።

በመሆኑም እነዚህ እሴቶች ቀጣይነት እንዲኖራቸው የአሁኑ ትውልድ ሀላፊነት እንዳለበትም አመላክተዋል።

በስልጠና መድረኩ የሚዲያ አመራሮችና ባለሙያዎች እየተሳተፉ ይገኛል።

ዘጋቢ፡ ረድኤት እግዜሩ – ከወልቂጤ ጣቢያችን