ሀገራችን በአህጉርም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ የምትታወቅባቸው በርካታ እሴቶች ቀጣይነት እንዲኖራቸው የአሁኑ ትውልድ ሀላፊነት እንዳለበት የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አስገነዘበ
ዩኒቨርሲቲው የሀገር በቀል ቋንቋና ባህልን ለማጎልበት ያለመ ስልጠና ለሚዲያ ባለሙያዎች እየሰጠ ይገኛል።
ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ሀብቴ ዱላ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ በአህጉርም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ የምትታወቅባቸው የበርካታ እሴቶች ባለቤት ናት ብለዋል።
በመሆኑም እነዚህ እሴቶች ቀጣይነት እንዲኖራቸው የአሁኑ ትውልድ ሀላፊነት እንዳለበትም አመላክተዋል።
በስልጠና መድረኩ የሚዲያ አመራሮችና ባለሙያዎች እየተሳተፉ ይገኛል።
ዘጋቢ፡ ረድኤት እግዜሩ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል