ሀገራችን በአህጉርም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ የምትታወቅባቸው በርካታ እሴቶች ቀጣይነት እንዲኖራቸው የአሁኑ ትውልድ ሀላፊነት እንዳለበት የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አስገነዘበ
ዩኒቨርሲቲው የሀገር በቀል ቋንቋና ባህልን ለማጎልበት ያለመ ስልጠና ለሚዲያ ባለሙያዎች እየሰጠ ይገኛል።
ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ሀብቴ ዱላ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ በአህጉርም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ የምትታወቅባቸው የበርካታ እሴቶች ባለቤት ናት ብለዋል።
በመሆኑም እነዚህ እሴቶች ቀጣይነት እንዲኖራቸው የአሁኑ ትውልድ ሀላፊነት እንዳለበትም አመላክተዋል።
በስልጠና መድረኩ የሚዲያ አመራሮችና ባለሙያዎች እየተሳተፉ ይገኛል።
ዘጋቢ፡ ረድኤት እግዜሩ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ