ሀገራችን በአህጉርም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ የምትታወቅባቸው በርካታ እሴቶች ቀጣይነት እንዲኖራቸው የአሁኑ ትውልድ ሀላፊነት እንዳለበት የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አስገነዘበ
ዩኒቨርሲቲው የሀገር በቀል ቋንቋና ባህልን ለማጎልበት ያለመ ስልጠና ለሚዲያ ባለሙያዎች እየሰጠ ይገኛል።
ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ሀብቴ ዱላ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ በአህጉርም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ የምትታወቅባቸው የበርካታ እሴቶች ባለቤት ናት ብለዋል።
በመሆኑም እነዚህ እሴቶች ቀጣይነት እንዲኖራቸው የአሁኑ ትውልድ ሀላፊነት እንዳለበትም አመላክተዋል።
በስልጠና መድረኩ የሚዲያ አመራሮችና ባለሙያዎች እየተሳተፉ ይገኛል።
ዘጋቢ፡ ረድኤት እግዜሩ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ
ሁሉም ሰው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በቀጣይ የሚያስተዳድረውን መንግስት መምረጥ እንዲችል የምርጫ ካርድ በወቅቱ መያዝ እንደሚጠበቅበት ተገለጸ