በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኣሪ ዞን ትምህርት መምሪያ የ2017 ዓ.ም የጎልማሶች ትምህርት የብርሃን ምዘናን በ1 መቶ 12 ጣቢያዎች አካሂዷል
የማንበብና የመፃፍ ችግርን ለመቅረፍ የተቀናጀ ተግባር ተኮር የጎልማሶች ትምህርት የላቀ ሚና እንዳለው በምዘናው የተሳተፉ ጎልማሶች ገልፀዋል።
የጎልማሶችና መደበኛ ያልሆኑ የትምህርት ዘርፍ የትምህርት ብርሃን ምዘናው የማንበብ፣ የመፃፍና የማስላት ችግራቸውን እንደቀረፈላቸው በምዘናው ወቅት ካነጋገርናቸው ጎልማሶች መካከል አቶ ደምሴ መንገሻ እና ወይዘሮ ካሰች አየለ ገልፀዋል።
በኣሪ ዞን ትምህርት መምሪያ የጎልማሶች ትምህርት ዳይሬክተር ወይዘሮ ማስረሻ ሙላት፤ የትምህርት ብርሃን ምዘና ዓላማን ገልፀው ለዘርፉ ውጤታማነት የባለድርሻ አካላት ተሳትፎና ቁርጠኝነት ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል።
የኣሪ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ዳግም መኮንን፤ በኢትዮጵያ መደበኛ ትምህርት ረጅም ታሪክ እንዳለው ተናግረው መደበኛ ያልሆነ የተቀናጀ የጎልማሶች ትምህርት መደበኛውን በማገዝ መሀይምነትን ለማስወገድ ታልሞ የተዘጋጀ የትምህርት ለሁሉም ስትራቴጅክ አንዱ አካል ተድርጎ እየተሠራ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በዞኑ 1323 ወንድ 1643 ሴት በአጠቃላይ 2966 ጎልማሶች በ1 መቶ 12 ጣቢያዎች የብርሃን ምዘናውን መቀበላቸውን ኃላፊው ገልፀው፤ የጎልማሶች ትምህርትን ለማጠናከር ከአመለካከት ጀምሮ ያሉ በርካታ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ እየተሠራ እንዳለም አስረድተዋል።
ዘጋቢ፡ ተመስገን አሰፋ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል