ሀዋሳ፡ ግንቦት 20/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የኣሪ ዞን ሐይማኖት ተቋማት ጉባኤ ከወርልድ ቪዥን ግብረሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ከወረዳና ከተማ አሰተዳደር የሀይማኖት ተቋማት እና ባለድርሻ አካላት ጋር የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት መደረክ ተካሄዷል ።
የውይይት መድረኩ በአባቶች ፀሎትና ምርቃት ነው የተጀመረው፡፡
በውይይት መደረኩ መልዕክት ያስተላለፉት የኣሪ ዞን ሠላምና ፀጥታ አስተዳደር መምሪያ ሃላፊ አቶ ማታዶ በርቢ፥ የሐይማኖት ተቋማት በህዝቡ መሀል ሠላምና አብሮነት እንዲሰፍን ላደረጉት አሰተዋጽኦ ምስጋና አቅረበው ቀጣይም የተለመደው ተግባር እንዲጠናከር ጥሪ አቀረበዋል ።
በውይይት መደረኩ የ2017 ዓም የሀይማኖት ተቋማት ፎረም በሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳደር የተሠሩ ሥራዎች ሪፖሪት የቀረበ ሲሆን፥ የ2018 ዓ.ም ዕቅድ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል።
በሰነዱ መነሻ ከተሳታፍዎች መካከል አቶ ኡመርዲን ግርማ አቶ ካሳሁን ጠቃይና ሌሎችም በሰጡት አስተያየት የተሠሩ ስራዎች ጥሩ መሆናቸውን ገልፀው በቀጣይ የሀይማኖት ፎረሙ በልዩነት ውስጥ ያለውን አንድነትና መተሳሰብ በማስረፅ በኩል ትኩረት እንድሰጥበት ጠይቀዋል።
የኣሪ ዞን ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ስመኝ ተስፋዬ በበኩላቸው፥ የሀይማኖት ተቋማት ፎረም የህዝብ መሪ እንደመሆኑ የህዝብ ፍላጎት ላይ የተመሠረተ ባህልንና ሥርዓትን በተከተለ ሁሉን እኩል በማሳተፍ መምራት የሚገባው ጠቁመዋል፡፡
ኣሪ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ጉራልቅ ይዥማልቅ፥ ልማትና ዴሞክራሲ የሚረጋገጠው በሠላም መሆኑ በቀጣይም ለሠላም የሚያበረክቱትን አስተዋጾኦ እንዲያጠናክሩና ለአከባቢና ለሀገር እንዲተጉ ጠይቀዋል።
ዘጋቢ፡ ደፋሩ ስፍታዬ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ