ሀዋሳ፡ ግንቦት 20/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የኣሪ ዞን ሐይማኖት ተቋማት ጉባኤ ከወርልድ ቪዥን ግብረሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ከወረዳና ከተማ አሰተዳደር የሀይማኖት ተቋማት እና ባለድርሻ አካላት ጋር የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት መደረክ ተካሄዷል ።
የውይይት መድረኩ በአባቶች ፀሎትና ምርቃት ነው የተጀመረው፡፡
በውይይት መደረኩ መልዕክት ያስተላለፉት የኣሪ ዞን ሠላምና ፀጥታ አስተዳደር መምሪያ ሃላፊ አቶ ማታዶ በርቢ፥ የሐይማኖት ተቋማት በህዝቡ መሀል ሠላምና አብሮነት እንዲሰፍን ላደረጉት አሰተዋጽኦ ምስጋና አቅረበው ቀጣይም የተለመደው ተግባር እንዲጠናከር ጥሪ አቀረበዋል ።
በውይይት መደረኩ የ2017 ዓም የሀይማኖት ተቋማት ፎረም በሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳደር የተሠሩ ሥራዎች ሪፖሪት የቀረበ ሲሆን፥ የ2018 ዓ.ም ዕቅድ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል።
በሰነዱ መነሻ ከተሳታፍዎች መካከል አቶ ኡመርዲን ግርማ አቶ ካሳሁን ጠቃይና ሌሎችም በሰጡት አስተያየት የተሠሩ ስራዎች ጥሩ መሆናቸውን ገልፀው በቀጣይ የሀይማኖት ፎረሙ በልዩነት ውስጥ ያለውን አንድነትና መተሳሰብ በማስረፅ በኩል ትኩረት እንድሰጥበት ጠይቀዋል።
የኣሪ ዞን ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ስመኝ ተስፋዬ በበኩላቸው፥ የሀይማኖት ተቋማት ፎረም የህዝብ መሪ እንደመሆኑ የህዝብ ፍላጎት ላይ የተመሠረተ ባህልንና ሥርዓትን በተከተለ ሁሉን እኩል በማሳተፍ መምራት የሚገባው ጠቁመዋል፡፡
ኣሪ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ጉራልቅ ይዥማልቅ፥ ልማትና ዴሞክራሲ የሚረጋገጠው በሠላም መሆኑ በቀጣይም ለሠላም የሚያበረክቱትን አስተዋጾኦ እንዲያጠናክሩና ለአከባቢና ለሀገር እንዲተጉ ጠይቀዋል።
ዘጋቢ፡ ደፋሩ ስፍታዬ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል