የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ፣ የፌደራልና የክልሎች ልዑክ በሀላባ ዞን የመስክ ምልከታ እያደረገ ነው
ሀዋሳ፡ ግንቦት 20/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ፣ የፌደራልና የክልሎች ልዑክ በሀላባ ዞን የተሰሩ የልማት ስራዎችን ምልከታ እያደረገ ነው።
ሶስተኛ ቀኑን የያዘው የሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም የሀረሪና የጋምቤላ ክልል ሴቶች ህፃናት ቢሮ አመራሮችና ባለሙያዎች ጉብኝት በሀላባ ዞን በሴቶች ህብረት ማህበራት እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን እየተመለከተ ነው።
በዞኑ ዌራጂዶ ወረዳ ሲምቢጣ ቀበሌ የለማ የፍራፍሬና አትክልት ልማት ስራን ተመልክተዋል።
በዞኑ ሴቶች ህብረት ማህበራት እየተሰሩ ያሉ የግብርና ስራዎችን ተዘዋውረው በመጎብኘት ላይ ናቸው፡፡
ዘጋቢ፡ ባዬ በልስቲ

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ