የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ፣ የፌደራልና የክልሎች ልዑክ በሀላባ ዞን የመስክ ምልከታ እያደረገ ነው

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ፣ የፌደራልና የክልሎች ልዑክ በሀላባ ዞን የመስክ ምልከታ እያደረገ ነው

ሀዋሳ፡ ግንቦት 20/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ፣ የፌደራልና የክልሎች ልዑክ በሀላባ ዞን የተሰሩ የልማት ስራዎችን ምልከታ እያደረገ ነው።

ሶስተኛ ቀኑን የያዘው የሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም የሀረሪና የጋምቤላ ክልል ሴቶች ህፃናት ቢሮ አመራሮችና ባለሙያዎች ጉብኝት በሀላባ ዞን በሴቶች ህብረት ማህበራት እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን እየተመለከተ ነው።

በዞኑ ዌራጂዶ ወረዳ ሲምቢጣ ቀበሌ የለማ የፍራፍሬና አትክልት ልማት ስራን ተመልክተዋል።

በዞኑ ሴቶች ህብረት ማህበራት እየተሰሩ ያሉ የግብርና ስራዎችን ተዘዋውረው በመጎብኘት ላይ ናቸው፡፡

ዘጋቢ፡ ባዬ በልስቲ