የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ፣ የፌደራልና የክልሎች ልዑክ በሀላባ ዞን የመስክ ምልከታ እያደረገ ነው
ሀዋሳ፡ ግንቦት 20/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ፣ የፌደራልና የክልሎች ልዑክ በሀላባ ዞን የተሰሩ የልማት ስራዎችን ምልከታ እያደረገ ነው።
ሶስተኛ ቀኑን የያዘው የሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም የሀረሪና የጋምቤላ ክልል ሴቶች ህፃናት ቢሮ አመራሮችና ባለሙያዎች ጉብኝት በሀላባ ዞን በሴቶች ህብረት ማህበራት እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን እየተመለከተ ነው።
በዞኑ ዌራጂዶ ወረዳ ሲምቢጣ ቀበሌ የለማ የፍራፍሬና አትክልት ልማት ስራን ተመልክተዋል።
በዞኑ ሴቶች ህብረት ማህበራት እየተሰሩ ያሉ የግብርና ስራዎችን ተዘዋውረው በመጎብኘት ላይ ናቸው፡፡
ዘጋቢ፡ ባዬ በልስቲ

More Stories
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ
ሁሉም ሰው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በቀጣይ የሚያስተዳድረውን መንግስት መምረጥ እንዲችል የምርጫ ካርድ በወቅቱ መያዝ እንደሚጠበቅበት ተገለጸ