የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ፣ የፌደራልና የክልሎች ልዑክ በሀላባ ዞን የመስክ ምልከታ እያደረገ ነው
ሀዋሳ፡ ግንቦት 20/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ፣ የፌደራልና የክልሎች ልዑክ በሀላባ ዞን የተሰሩ የልማት ስራዎችን ምልከታ እያደረገ ነው።
ሶስተኛ ቀኑን የያዘው የሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም የሀረሪና የጋምቤላ ክልል ሴቶች ህፃናት ቢሮ አመራሮችና ባለሙያዎች ጉብኝት በሀላባ ዞን በሴቶች ህብረት ማህበራት እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን እየተመለከተ ነው።
በዞኑ ዌራጂዶ ወረዳ ሲምቢጣ ቀበሌ የለማ የፍራፍሬና አትክልት ልማት ስራን ተመልክተዋል።
በዞኑ ሴቶች ህብረት ማህበራት እየተሰሩ ያሉ የግብርና ስራዎችን ተዘዋውረው በመጎብኘት ላይ ናቸው፡፡
ዘጋቢ፡ ባዬ በልስቲ
More Stories
የኢፌዲሪ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ከ82 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ መቆርቆር ቀበሌ ያስገነባው የንጹህ መጠ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
የኡዱሂያ የዕርድ ስርዓት….የአብሮነት ነፀብራቅ
በቅርቡ በሚሰጠው የ6ኛ እና የ8ኛ ክልላዊ ፈተና ላይ ከ53 ሺህ በላይ ተማሪዎች ለፈተና እንደሚቀርቡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀዲያ ዞን ትምህርት መመሪያ አስታወቀ