ሁለተኛ ዙር የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ከግንቦት 22 ጀምሮ ለተከታታይ 4 ቀናት እንደሚሰጥ ተገለጸ
ሀወሳ፡ ግንቦት 19/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ሁለተኛ ዙር የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ከግንቦት 22 ጀምሮ ለተከታታይ 4 ቀናት እንደሚሰጥ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የቀቤና ልዩ ወረዳ ጤና ፅ/ቤት አስታወቀ።
በሁለተኛ ዙር የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ከ17 ሺህ በላይ ህፃናት እንደሚወስዱ ፅ/ቤቱ ገልጿል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የቀቤና ልዩ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብድልኸይ ኑርሀሰን ለጣቢያችን በሰጡት መግለጫ የልጅነት ልምሻ ሕፃናትን ለሕመም፣ ለአካል ጉዳት እና ለተለያዩ በሽታዎች ከሚዳርጉ በሽታዎች አንዱ መሆኑን ጠቁመዋል።
በአገር አቀፍ፣ በክልል ብሎም በልዩ ወረዳዉ በሽታዉን አስቀድሞ ለመካለከል ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝም ገልፀዋል።
በቀቤና ልዩ ወረዳ በተያዘዉ በጀት አመት የመከላከያ ክትባቱን ከ13 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ህፃናት መሰጠቱን ያነሱት ኃላፊዉ ዉጤታማ እንደነበረም ተናግረዋል።
ከግንቦት 22 ጀምሮ ለተከታታይ 4 ቀናት ለሚሰጠዉ ለሁለተኛ ዙር የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ዘመቻ ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን በመግለፅ ከ17 ሺህ በላይ ህፃናት ክትባቱን እንደሚወስዱ አቶ አብድልኸይ ጠቁመዋል።
ከክትባቱ ጎን ለጎን ሌሎች የጤና ጉዳዮች የህጻናት የምግብ እጥረት ልየታ፣ የመደበኛ ክትባት አገልግሎት ያላገኙና ያቋረጡ ህጻናት ልየታ፣ የማህፀን ዉልቃት ያለባቸዉ እናቶች ልየታ እንደሚደረግም አስረድተዋል።
የሚዲያና የኮምዩንኬሽን አካላት ለስራዉ ዉጤታማነት የበኩላቸዉን አስተዋፆ ማበርከት እንዳለባቸዉና ህብረተሰቡም እድሜያቸዉ ከ59 ወራት በታች የሆኑ ህፃናትን ማስከተብ እንዳለባቸዉ ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡ ሪያድ ሙህዲን – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ