በስራና ክህሎት ሚኒስቴር የስራ ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ የተመራ ቡድን የ2017 በጀት አመት አስር ወራት የስራ እንቅስቃሴን በጉራጌ ዞንና በወልቂጤ ሳታላይት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ምልከታ እያደረገ ነው
ሀዋሳ፡ ግንቦት 19/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በስራና ክህሎት ሚኒስቴር የስራ ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ የተመራ ቡድን የ2017 በጀት አመት አስር ወራት የስራ እንቅስቃሴ የክህሎት ልማት፣ በስራ ዕድል ፈጠራ እና በስራ ላይ ደህንነት እንዲሁም በተቋም ግንባታ ዙሪያ በጉራጌ ዞንና በወልቂጤ ሳተላይት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ምልከታ እያደረገ ነው።
በዞኑ በመስኖ ልማት በበልግና በመኸር ሰብልና በከብት እርባታ የተሰሩ ስራዎች ጉብኝት የተደረገ ሲሆን ኢንተርፕራይዞች በአመት ሶስት ጊዜ በማምረትና በተሰማሩባቸው ዘርፎች ውጤታማ መሆን ከተቻለ ሰፋፊ ማሳዎችን በማልማት ወደ ኢንቨስትመንት ማደግ እንደሚቻል በጉብኝቱ ተገልጿል::
የወልቂጤ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከፕሮጀክቶች ጋር በመቀናጀት እየሰጠ ያለው ክህሎት ነክ ስልጠና እና የውስጥ ገቢን ለማሳደግ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችንም ተመልክተዋል።
በጉብኝቱ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ሀላፊ ሙስጠፋ ኢሳን ጨምሮ የክልልና የዞን አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ሄኖክ ተክሌ – ከወልቂጤ ጣቢያችን
More Stories
ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፍ እያስመዘገበች ላለችው የዕድገት ጉዞ ቀጣይነት የትምህርት ተቋማት ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ለትምህርት ጥራት በቁርጠኝነት ሊሰሩ ይገባል ሲል የጋሞ ዞን አስተዳደር አሳሰበ
በትምህርት ዘርፍ የተገኙ ውጤቶችን አጽንቶ ማስቀጠል እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ወ/ሮ ፀሐይ ወራሳ ገለፁ
በኮንታ ዞን ጳጉሜን 1 – የጽናት ቀን በተለያዩ ሁነቶች ተከብሯል