በስራና ክህሎት ሚኒስቴር የስራ ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ የተመራ ቡድን የ2017 በጀት አመት አስር ወራት የስራ እንቅስቃሴን በጉራጌ ዞንና በወልቂጤ ሳታላይት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ምልከታ እያደረገ ነው
ሀዋሳ፡ ግንቦት 19/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በስራና ክህሎት ሚኒስቴር የስራ ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ የተመራ ቡድን የ2017 በጀት አመት አስር ወራት የስራ እንቅስቃሴ የክህሎት ልማት፣ በስራ ዕድል ፈጠራ እና በስራ ላይ ደህንነት እንዲሁም በተቋም ግንባታ ዙሪያ በጉራጌ ዞንና በወልቂጤ ሳተላይት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ምልከታ እያደረገ ነው።
በዞኑ በመስኖ ልማት በበልግና በመኸር ሰብልና በከብት እርባታ የተሰሩ ስራዎች ጉብኝት የተደረገ ሲሆን ኢንተርፕራይዞች በአመት ሶስት ጊዜ በማምረትና በተሰማሩባቸው ዘርፎች ውጤታማ መሆን ከተቻለ ሰፋፊ ማሳዎችን በማልማት ወደ ኢንቨስትመንት ማደግ እንደሚቻል በጉብኝቱ ተገልጿል::
የወልቂጤ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከፕሮጀክቶች ጋር በመቀናጀት እየሰጠ ያለው ክህሎት ነክ ስልጠና እና የውስጥ ገቢን ለማሳደግ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችንም ተመልክተዋል።
በጉብኝቱ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ሀላፊ ሙስጠፋ ኢሳን ጨምሮ የክልልና የዞን አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ሄኖክ ተክሌ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ