በስራና ክህሎት ሚኒስቴር የስራ ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ የተመራ ቡድን የ2017 በጀት አመት አስር ወራት የስራ እንቅስቃሴን በጉራጌ ዞንና በወልቂጤ ሳታላይት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ምልከታ እያደረገ ነው
ሀዋሳ፡ ግንቦት 19/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በስራና ክህሎት ሚኒስቴር የስራ ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ የተመራ ቡድን የ2017 በጀት አመት አስር ወራት የስራ እንቅስቃሴ የክህሎት ልማት፣ በስራ ዕድል ፈጠራ እና በስራ ላይ ደህንነት እንዲሁም በተቋም ግንባታ ዙሪያ በጉራጌ ዞንና በወልቂጤ ሳተላይት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ምልከታ እያደረገ ነው።
በዞኑ በመስኖ ልማት በበልግና በመኸር ሰብልና በከብት እርባታ የተሰሩ ስራዎች ጉብኝት የተደረገ ሲሆን ኢንተርፕራይዞች በአመት ሶስት ጊዜ በማምረትና በተሰማሩባቸው ዘርፎች ውጤታማ መሆን ከተቻለ ሰፋፊ ማሳዎችን በማልማት ወደ ኢንቨስትመንት ማደግ እንደሚቻል በጉብኝቱ ተገልጿል::
የወልቂጤ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከፕሮጀክቶች ጋር በመቀናጀት እየሰጠ ያለው ክህሎት ነክ ስልጠና እና የውስጥ ገቢን ለማሳደግ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችንም ተመልክተዋል።
በጉብኝቱ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ሀላፊ ሙስጠፋ ኢሳን ጨምሮ የክልልና የዞን አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ሄኖክ ተክሌ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ
ሁሉም ሰው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በቀጣይ የሚያስተዳድረውን መንግስት መምረጥ እንዲችል የምርጫ ካርድ በወቅቱ መያዝ እንደሚጠበቅበት ተገለጸ