በስራና ክህሎት ሚኒስቴር የስራ ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ የተመራ ቡድን የ2017 በጀት አመት አስር ወራት የስራ እንቅስቃሴን በጉራጌ ዞንና በወልቂጤ ሳታላይት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ምልከታ እያደረገ ነው
ሀዋሳ፡ ግንቦት 19/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በስራና ክህሎት ሚኒስቴር የስራ ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ የተመራ ቡድን የ2017 በጀት አመት አስር ወራት የስራ እንቅስቃሴ የክህሎት ልማት፣ በስራ ዕድል ፈጠራ እና በስራ ላይ ደህንነት እንዲሁም በተቋም ግንባታ ዙሪያ በጉራጌ ዞንና በወልቂጤ ሳተላይት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ምልከታ እያደረገ ነው።
በዞኑ በመስኖ ልማት በበልግና በመኸር ሰብልና በከብት እርባታ የተሰሩ ስራዎች ጉብኝት የተደረገ ሲሆን ኢንተርፕራይዞች በአመት ሶስት ጊዜ በማምረትና በተሰማሩባቸው ዘርፎች ውጤታማ መሆን ከተቻለ ሰፋፊ ማሳዎችን በማልማት ወደ ኢንቨስትመንት ማደግ እንደሚቻል በጉብኝቱ ተገልጿል::
የወልቂጤ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከፕሮጀክቶች ጋር በመቀናጀት እየሰጠ ያለው ክህሎት ነክ ስልጠና እና የውስጥ ገቢን ለማሳደግ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችንም ተመልክተዋል።
በጉብኝቱ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ሀላፊ ሙስጠፋ ኢሳን ጨምሮ የክልልና የዞን አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ሄኖክ ተክሌ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል