ምክር ቤቱ ነገ 32ኛ መደበኛ ስብሰባውን ያካሄዳል

ምክር ቤቱ ነገ 32ኛ መደበኛ ስብሰባውን ያካሄዳል

6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 32ኛ መደበኛ ስብሰባ ነገ ይካሄዳል።

ነገ በሚደረገው መደበኛ ስብሰባ ምክር ቤቱ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ከምክር ቤት አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች የሚሰጡትን መልስና ማበራሪያ የሚያደምጥ ይሆናል።

በተጨማሪም የሥርዓተ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ እንዲሁም የባለብዙ ተዋንያን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅን መርምሮ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ ይመራል ተብሎ ይጠበቃል።

ምንጭ ፡   የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት