ሀዋሳ፣ ግንቦት 15/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ “ትውልድ በመምህር ይቀረጻል ፤ ሀገር በትምህርት ይበለጽጋል” በሚል መሪ ቃል የመምህራን ውይይት እየተካሄደ ነው።
የዩኒቨርሲቲው ተጠባባቂ ፕሬዝደንት ዶክተር ደገለ ኤርገኖ፤ የመድረኩ ዓላማ የመምህራንን ሀሳብ ለማድመጥና እርስ በእርስ መወያየት የሚችሉበትን ሁኔታ መፍጠር ነው ብለዋል።
መንግስት ለሚሰራቸው ስራዎች ግብዓት የሚሆኑ ሀሳቦችን ከምሁራን ለማግኘትና ተግባራዊ ለማድረግ በሀገር-አቀፍ ደረጃ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር ውይይት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰመስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው፤ መምህርነት ለሀገር ጠቃሚ ዜጎችን የሚያፈሩበት የተከበረ ሙያ ነው ብለዋል።
ሀገራዊ ለውጡ አሁን የደረሰበትን ደረጃና ቀጣይ አቅጣጫዎችን በሚመለከት ባቀረቡት የመወያያ ሰነድ አሰባሳቢ ትርክትን ለመፍጠርና ህብረ-ብሔራዊነትን ለማፅናት የመምህራን አስተዋፅኦ ከፍተኛ ነው ብለዋል።
የትምህርት ዘርፍ ሙያዊ ነፃነቱ ተጠብቆ እንዲቀጥልና ሀገርን መምራት የሚችሉ ምሁራንን ለማፍራት እንዲቻል በመንግስት ደረጃ ትኩረት ተሰጥቶ መሰራቱን ነው የተናገሩት።
በትምሀርት ዘርፍ ከተከናወኑ የለውጥ ስራዎች መካከል ሙያዊ ነፃነትን ለማስከበር፣ የፈተና አሰጣጥንና አጠቃላይ የትምህርት ስርዓቱን ለማሻሻል መሰራቱን ጠቅሰዋል።
በዚህም የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ ተጨባጭ ለውጥ መታየት ጀምሯል ነው ያሉት።
የተወዘፉ የትምህርት ዘርፍ ችግሮችን በመለየት ባለፉት ሰባት ዓመታት ለውጥ መታየቱን ገልፀዋል።
በመድረኩ ሀገራዊ ነባራዊ ሁኔታዎችን እና የቀጣይ ስራ አቅጣጫዎችን የሚመለከት ሰነድ ቀርቦ ውይይት እየተደረገበት ይገኛል።
ዘጋቢ፡ ዮሐንስ ክፍሌ – ከቦንጋ ጣቢያችን
More Stories
የኢፌዲሪ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ከ82 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ መቆርቆር ቀበሌ ያስገነባው የንጹህ መጠ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
የኡዱሂያ የዕርድ ስርዓት….የአብሮነት ነፀብራቅ
በቅርቡ በሚሰጠው የ6ኛ እና የ8ኛ ክልላዊ ፈተና ላይ ከ53 ሺህ በላይ ተማሪዎች ለፈተና እንደሚቀርቡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀዲያ ዞን ትምህርት መመሪያ አስታወቀ