የዉይይቱ ዋና ዓላማ በጤና ልማት ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶች ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል ፣ ጉድለቶችን ደግሞ ፈጥኖ ለማረም እና በቀጣይ የተሻለ ዉጤት ለማስመዝገብ ከባለድርሻ አካላት ጋር የጋራ መግባባት መፍጠር ነዉ ተብሏል።
የየም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሽመልስ እጅጉ እንደገለፁት ባለፉት አመታት መንግስት በጤናዉ ልማት ዘርፍ አገልግሎቱን ተደራሽ ለማድረግና ጥራቱን ከማስጠበቅ ረገድ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በመስራት የተሻለ ለውጥ መመዝገቡን ገልጸዋል።
በተጨማሪም በጤና ልማት ዘርፍ የሚስተዋሉ የደመወዝ ጭማሪ፣ የትርፍ ሰዓት ክፊያ፣ የግብዓት እጥረት እና ሌሎች የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መንግስት በአጭር፣ በመካከለኛ እና በረጅም ጊዜ ለመፍታት አቅዶ እየሰራ መሆኑም አመላክተዋል።
በዘርፉ በአፈፃፀም ረገድ የሚታዩ ጉድለቶችን ፈጥኖ ለመፍታት እየተሰራ ያለዉ ተግባር ውጤታማ እንዲሆን ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸዉን አስተዋፆ ማበርከት እንዳለባቸዉ አስተዳዳሪው ጠቅሰዋል፡፡
የየም ዞን ብልጽግና ፖርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብርሃም ዝናብ በዞኑ ያሉ ጤና ባለሙያዎች በገቡት ቃል መሠረት ቅድሚያ ለሕዝብ ጤና የሚሠሩ ናቸው ብለዋል።
የጤና ባለሙያው እያቀረበ ያለውን ትክክለኛ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠትከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየሰራን ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡
የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሠናይ ረጉ፤ ባለሙያዎች የሚያነሱትን ጥያቄዎች ለመመለስ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተሠራ ነው ብለዋል ።
የውይይቱ ተሳታፊዎች በጤናው ዘርፍ ከሚታዩ ችግሮች መካከል የደመወዝ ጭማሪ፣ የትፍ ሰዓት አገልግሎት ክፍያ ያለመከፈል፣ የተቋማት እድሣት ያለመደረግ፣ የደረጃ ዕድገት እና ዝውውር እንድሁም ከበጀት ጋር በተያያዘ የሚገጥሙ ችግሮች እንድፈቱ ጥረት መደረግ አለበት ብለዋል ።
የውይይቱ ተሳታፊዎች በክልል መንግስትና በዞን እየተሰሩ ያሉ የኮሾ ሁለገብ የፍራፍሬ መሸጫ ማዕከል ግንባታ፣ የሳጃ ከተማ ኮርደር ልማት ሥራ እንዲሁም ኢንተርፕራይዝና ማኑፋክቸርንግ ዘርፍ ሥራዎች ጉብኝት ተደርጓል።
ዘጋቢ፡- ማሙዬ ፊጣ ከወልቂጤ ጣቢያችን
More Stories
የኢፌዲሪ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ከ82 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ መቆርቆር ቀበሌ ያስገነባው የንጹህ መጠ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
የኡዱሂያ የዕርድ ስርዓት….የአብሮነት ነፀብራቅ
በቅርቡ በሚሰጠው የ6ኛ እና የ8ኛ ክልላዊ ፈተና ላይ ከ53 ሺህ በላይ ተማሪዎች ለፈተና እንደሚቀርቡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀዲያ ዞን ትምህርት መመሪያ አስታወቀ