የዉይይቱ ዋና ዓላማ በጤና ልማት ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶች ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል ፣ ጉድለቶችን ደግሞ ፈጥኖ ለማረም እና በቀጣይ የተሻለ ዉጤት ለማስመዝገብ ከባለድርሻ አካላት ጋር የጋራ መግባባት መፍጠር ነዉ ተብሏል።
የየም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሽመልስ እጅጉ እንደገለፁት ባለፉት አመታት መንግስት በጤናዉ ልማት ዘርፍ አገልግሎቱን ተደራሽ ለማድረግና ጥራቱን ከማስጠበቅ ረገድ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በመስራት የተሻለ ለውጥ መመዝገቡን ገልጸዋል።
በተጨማሪም በጤና ልማት ዘርፍ የሚስተዋሉ የደመወዝ ጭማሪ፣ የትርፍ ሰዓት ክፊያ፣ የግብዓት እጥረት እና ሌሎች የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መንግስት በአጭር፣ በመካከለኛ እና በረጅም ጊዜ ለመፍታት አቅዶ እየሰራ መሆኑም አመላክተዋል።
በዘርፉ በአፈፃፀም ረገድ የሚታዩ ጉድለቶችን ፈጥኖ ለመፍታት እየተሰራ ያለዉ ተግባር ውጤታማ እንዲሆን ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸዉን አስተዋፆ ማበርከት እንዳለባቸዉ አስተዳዳሪው ጠቅሰዋል፡፡
የየም ዞን ብልጽግና ፖርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብርሃም ዝናብ በዞኑ ያሉ ጤና ባለሙያዎች በገቡት ቃል መሠረት ቅድሚያ ለሕዝብ ጤና የሚሠሩ ናቸው ብለዋል።
የጤና ባለሙያው እያቀረበ ያለውን ትክክለኛ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠትከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየሰራን ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡
የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሠናይ ረጉ፤ ባለሙያዎች የሚያነሱትን ጥያቄዎች ለመመለስ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተሠራ ነው ብለዋል ።
የውይይቱ ተሳታፊዎች በጤናው ዘርፍ ከሚታዩ ችግሮች መካከል የደመወዝ ጭማሪ፣ የትፍ ሰዓት አገልግሎት ክፍያ ያለመከፈል፣ የተቋማት እድሣት ያለመደረግ፣ የደረጃ ዕድገት እና ዝውውር እንድሁም ከበጀት ጋር በተያያዘ የሚገጥሙ ችግሮች እንድፈቱ ጥረት መደረግ አለበት ብለዋል ።
የውይይቱ ተሳታፊዎች በክልል መንግስትና በዞን እየተሰሩ ያሉ የኮሾ ሁለገብ የፍራፍሬ መሸጫ ማዕከል ግንባታ፣ የሳጃ ከተማ ኮርደር ልማት ሥራ እንዲሁም ኢንተርፕራይዝና ማኑፋክቸርንግ ዘርፍ ሥራዎች ጉብኝት ተደርጓል።
ዘጋቢ፡- ማሙዬ ፊጣ ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
የግል እና የጋራ መጸዳጃ ቤቶችን በተገቢው በመጠቀም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስገነዘበ
12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በተቋማት የድርጊት መርሐ-ግብርና በፀደቀላቸው በጀት መሠረት ማሰራጨቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ አስታወቀ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡኢ ከተማ አስተዳደር እየተገነባ የሚገኘውን ብሉ ኤለፋንት ፋይበር ቦርድ ካምፓኒ ጎበኙ