በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ የተመራ የክልሉ የሁለቱ ምክር ቤቶች አፈ ጉባኤዎች ልዑክ የካራት ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅንና የካራት ማረሚያ ቤት ግንባታን ጎበኙ
የሀገሪቱን የኮሪደር ልማት ውጤታማ ለማድረግ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት የፈጠራ ስራቸውን ሊያጎለብቱ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ጠይቀዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ም/ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ የተመራ የክልሉ የሁለቱ ምክር ቤቶች አፈ ጉባኤዎች ልዑክ የካራት ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅንና የካራት ማረሚያ ቤት ግንባታ ጉብኝት አድርገዋል።
በጉብኝቱ ወቅት በዞኑ የሚገኙ ኢንተርፕራይዞችን ተጠቃሚነት በሚያረጋግጥ መልኩ የቴክኒክና ሙያ ተቋሙ የድርሻውን እንዲወጣ የጠየቁት ዋና አፈ ጉባኤው፤ የካራት ከተማ የኮሪደር ልማትን የሚያግዘው የቴራዞን ማምረት ስራው አበረታች ስለመሆኑም አመላክተዋል።
በካራት ከተማ ማረሚያ ተቋም ባለመኖሩ ምክንያት ህብረተሰቡ ታራሚን ለመጎብኘት አርባምንጭና ዝዋይ በሚያደርገው ጉዞ ለአላስፈላጊ ወጪና እንግልት ሲዳረግ መቆየቱም ተነግሯል።
ይህ አዲሱ የካራት ማረሚያ ተቋም ግንባታ በህብረተሰቡና በመንግስት የጋራ ትብብር እየተገነባ መሆኑም በጉብኝቱ ወቅት ተገልጿል።
ዘጋቢ፡ በኃይሉ ሙሉጌታ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

                
                                        
                                        
                                        
                                        
More Stories
እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ከዳር ለማድረስ በሚደረገው ርብርብ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሙዱላ ከተማ አስተዳደር ገለፀ
በትምህርት ሴክተር የመረጃ አያያዝ ውጤታማነት ዙሪያ በኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ
ሁሉንም የመማሪያ መጻሕፍት ባለማግኘታቸው በትምህርታቸው ላይ ጫና እየፈጠረባቸው መሆኑን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የቆንጋና ቆቄ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተናገሩ