በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ የተመራ የክልሉ የሁለቱ ምክር ቤቶች አፈ ጉባኤዎች ልዑክ የካራት ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅንና የካራት ማረሚያ ቤት ግንባታን ጎበኙ
የሀገሪቱን የኮሪደር ልማት ውጤታማ ለማድረግ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት የፈጠራ ስራቸውን ሊያጎለብቱ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ጠይቀዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ም/ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ የተመራ የክልሉ የሁለቱ ምክር ቤቶች አፈ ጉባኤዎች ልዑክ የካራት ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅንና የካራት ማረሚያ ቤት ግንባታ ጉብኝት አድርገዋል።
በጉብኝቱ ወቅት በዞኑ የሚገኙ ኢንተርፕራይዞችን ተጠቃሚነት በሚያረጋግጥ መልኩ የቴክኒክና ሙያ ተቋሙ የድርሻውን እንዲወጣ የጠየቁት ዋና አፈ ጉባኤው፤ የካራት ከተማ የኮሪደር ልማትን የሚያግዘው የቴራዞን ማምረት ስራው አበረታች ስለመሆኑም አመላክተዋል።
በካራት ከተማ ማረሚያ ተቋም ባለመኖሩ ምክንያት ህብረተሰቡ ታራሚን ለመጎብኘት አርባምንጭና ዝዋይ በሚያደርገው ጉዞ ለአላስፈላጊ ወጪና እንግልት ሲዳረግ መቆየቱም ተነግሯል።
ይህ አዲሱ የካራት ማረሚያ ተቋም ግንባታ በህብረተሰቡና በመንግስት የጋራ ትብብር እየተገነባ መሆኑም በጉብኝቱ ወቅት ተገልጿል።
ዘጋቢ፡ በኃይሉ ሙሉጌታ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ