በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ የተመራ የክልሉ የሁለቱ ምክር ቤቶች አፈ ጉባኤዎች ልዑክ የካራት ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅንና የካራት ማረሚያ ቤት ግንባታን ጎበኙ
የሀገሪቱን የኮሪደር ልማት ውጤታማ ለማድረግ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት የፈጠራ ስራቸውን ሊያጎለብቱ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ጠይቀዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ም/ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ የተመራ የክልሉ የሁለቱ ምክር ቤቶች አፈ ጉባኤዎች ልዑክ የካራት ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅንና የካራት ማረሚያ ቤት ግንባታ ጉብኝት አድርገዋል።
በጉብኝቱ ወቅት በዞኑ የሚገኙ ኢንተርፕራይዞችን ተጠቃሚነት በሚያረጋግጥ መልኩ የቴክኒክና ሙያ ተቋሙ የድርሻውን እንዲወጣ የጠየቁት ዋና አፈ ጉባኤው፤ የካራት ከተማ የኮሪደር ልማትን የሚያግዘው የቴራዞን ማምረት ስራው አበረታች ስለመሆኑም አመላክተዋል።
በካራት ከተማ ማረሚያ ተቋም ባለመኖሩ ምክንያት ህብረተሰቡ ታራሚን ለመጎብኘት አርባምንጭና ዝዋይ በሚያደርገው ጉዞ ለአላስፈላጊ ወጪና እንግልት ሲዳረግ መቆየቱም ተነግሯል።
ይህ አዲሱ የካራት ማረሚያ ተቋም ግንባታ በህብረተሰቡና በመንግስት የጋራ ትብብር እየተገነባ መሆኑም በጉብኝቱ ወቅት ተገልጿል።
ዘጋቢ፡ በኃይሉ ሙሉጌታ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል