የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የሁለቱ ምክር ቤቶች የጋራ ምክክር ፎረም በኮንሶ ዞን ካራት ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት እና የብሔረሰቦች ምክር ቤት የጋራ ምክክር ፎረም ላይ የተገኙት የክልሉ መንግስት ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ፤ የምክክር ፎረሙ የክልሉን ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ አጋዥ ስለመሆኑ ተናግረዋል።
በእውቀትና በሳይንስ የሚመሩ ምክር ቤቶች ይፈጠሩ ዘንድ የአቅም ማጎልበቻና የምክክር መድረኮች ፋይዳቸው የላቀ ስለመሆኑም ዋና አፈ ጉባኤው አውስተዋል።
ምክር ቤቶች የሰሩትን ስራ በሚገባ ገምግመው ውጤታማነቱን ማረጋገጥ ያስፈልግ ዘንድ መመካከሩ ወሳኝ ነው ያሉት አቶ አለማየሁ ባውዲ፤ በየደረጃው ያሉ የምክር ቤት አባላት ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባም አመላክተዋል።
የምክር ቤቶችን አቅም ማጎልበት የህዝቦችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ነው ያሉት ዋና አፈ ጉባኤው፤ ለዚህ ሀገራዊ ተልዕኮ ዝግጁ መሆን እንዳለባቸው መክረዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አዳማ ትንጳኤ እና የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ እንዲሁም የዞኖችና የከተማ አስተዳደር ምክር ቤቶች አፈ ጉባኤዎች ለሁለት ቀናት በሚቆየው የጋራ የምክክር መድረኮች ላይ እየተሳተፉ ይገኛል።
ዘጋቢ: በኃይሉ ሙሉጌታ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን
More Stories
የጽናት ቀንን ለኢትዮጵያ ሰላምና ደህንነት የታገሉና የተዋደቁትን በማሰብና በማመስገን ማክበር እንደሚገባ የካፋ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ደመላሽ ንጉሴ ገለጹ
ሀገራችንን ወደ ብልፅግና ለማድረስ የጽናት መንፈሳችንን ማደስ እንደሚገባ ተገለጸ
“ትንንሽ የሚመስሉ ስራዎች ለትልልቅ ዕድሎች በር ይከፍታሉ” – ወይዘሮ ህልውና ጌታቸው