የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የሁለቱ ምክር ቤቶች የጋራ ምክክር ፎረም በኮንሶ ዞን ካራት ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት እና የብሔረሰቦች ምክር ቤት የጋራ ምክክር ፎረም ላይ የተገኙት የክልሉ መንግስት ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ፤ የምክክር ፎረሙ የክልሉን ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ አጋዥ ስለመሆኑ ተናግረዋል።
በእውቀትና በሳይንስ የሚመሩ ምክር ቤቶች ይፈጠሩ ዘንድ የአቅም ማጎልበቻና የምክክር መድረኮች ፋይዳቸው የላቀ ስለመሆኑም ዋና አፈ ጉባኤው አውስተዋል።
ምክር ቤቶች የሰሩትን ስራ በሚገባ ገምግመው ውጤታማነቱን ማረጋገጥ ያስፈልግ ዘንድ መመካከሩ ወሳኝ ነው ያሉት አቶ አለማየሁ ባውዲ፤ በየደረጃው ያሉ የምክር ቤት አባላት ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባም አመላክተዋል።
የምክር ቤቶችን አቅም ማጎልበት የህዝቦችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ነው ያሉት ዋና አፈ ጉባኤው፤ ለዚህ ሀገራዊ ተልዕኮ ዝግጁ መሆን እንዳለባቸው መክረዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አዳማ ትንጳኤ እና የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ እንዲሁም የዞኖችና የከተማ አስተዳደር ምክር ቤቶች አፈ ጉባኤዎች ለሁለት ቀናት በሚቆየው የጋራ የምክክር መድረኮች ላይ እየተሳተፉ ይገኛል።
ዘጋቢ: በኃይሉ ሙሉጌታ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል