የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በዘላቂነት ለመፍታት በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ
ሀዋሳ፡ ግንቦት 11/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ህዝብ የሚያነሳቸው የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በዘላቂነት ለመፍታት የአጭርና የረጅም ጊዜ እቅድ ታቅዶ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የጉራጌ ዞን ምክር ቤት አስታወቀ፡፡
የጉራጌ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 12ኛ አመት 28ኛ መደበኛ ጉባኤው በወልቂጤ ከተማ እያካሄደ ነው።
የጉራጌ ዞን ምክር ቤት ምክትል አፈጉባኤ አቶ ኸይሩ መሀመድ መድረኩን በከፈቱበት ወቅት እንደገለፁት፥ በየደረጃው ህዝቡ የሚያነሳቸው የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በዘላቂነት ለመፍታት አጭርና የረጅም ጊዜ እቅድ ታቅዶ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተመላክቷል።
በተለይም እንደ ሃገር ያጋጠሙ ፈተናዎችን በፅናት በመሻገር በሁሉም ዘርፍ የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን ተመላክቷል።
ከዚህም ባሻገር እንደ ሃገር የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎች በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚና በማህበራዊ ዘርፍ እየመጣ ያለው ውጤት ተስፋ ሰጪ በመሆኑ እነዚህ ተግባራት የሃገሪቱ የብልፅግና ጉዞ ማሳያዎች መሆናቸውን አቶ ኸይሩ ተናግረዋል።
በዞኑ በአንዳንድ አካባቢዎች የነበሩ የፀጥታ ችግሮችን ለመፍታት የተጀመሩ ስራዎች አበረታች ቢሆኑም ዘላቂ ሰላም ለማስፈን አመራሩ በትኩረት መስራት እንዳለበት አስገንዝበዋል።
በበጀት አመቱ በክልል፣ በዞንና በወረዳ ደረጃ የተያዙት ፕሮጀክቶች ግንባታ በማጠናቀቅ ለህብረተሰቡ ቀልጣፋና ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።
ህብረተሰቡ በትምህርት፣ በመንገድ፣ በውኃ፣ በመብራት መሰረተ ልማቶችና በግብርናው ዘርፍ ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎች ማጠናከር ይገባል ብለዋል።
ዘጋቢ፡ እርካብነሽ ወ/ማርቆስ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ