በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ግንቦት 11/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ”የብልጽግና ጉዞዋችንና የንግዱ ማህበረሰብ ሚና” በሚል መሪ ቃል በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር የውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
መድረኩን በንግግር የከፈቱት የወልቂጤ ከተማ ከንቲባ አቶ ሙራድ ከድር፤ ባለፉት አመታት የንግዱ ማህበረሰብ ሀገራችን ተጋርጦባት የነበረውን የውስጥና የውጭ ፈተናዎችን በመጋፈጥ በድል ለመሻገር እያሳይ የነበረው ሚና ከፍተኛ እንደነበር ገልጸዋል።
የንግዱ ማህበረሰብ ኢኮኖሚያዊ ብልጽግና እንዲረጋገጥ የሚያደርገውን ተሳትፎ ይበልጥ በማጠናከር የልማት ጉዞዋችንን ማፋጠን ይጠበቅበታል ሲሉ ተናግረዋል።
በንግድ ስርዓቱ ፍትሐዊ የግብይት ስርዓትን ለመፍጠር መንግስት ችግሮችን ከነጋዴው ማህበረሰብ ጋር በጋራ እየፈታ ቀጣይነት እንዲኖረው ለማድረግ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።
የከተማው ማህበረሰብ ስራ ወዳድ፣ ሰላም ፈላጊ እና ከመንግስት ጎን በመሆን ልማትና ብልጽግና እንዲረጋገጥ አበክሮ የሚሰራ በመሆኑ ይህንን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አመላክተዋል።
በመድረኩ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ታደሰ ዋጄቦ፣ የጉራጌ ዞን ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አለማየሁ ገ/መስቀል፣ የዞኑ የሚመለከታቸው የመምሪያ ኃላፊዎች፣ የከተማው አመራሮች እና የንግዱ ማህበረሰብ ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ደጋጋ ኂሳቦ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ