በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ግንቦት 11/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ”የብልጽግና ጉዞዋችንና የንግዱ ማህበረሰብ ሚና” በሚል መሪ ቃል በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር የውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
መድረኩን በንግግር የከፈቱት የወልቂጤ ከተማ ከንቲባ አቶ ሙራድ ከድር፤ ባለፉት አመታት የንግዱ ማህበረሰብ ሀገራችን ተጋርጦባት የነበረውን የውስጥና የውጭ ፈተናዎችን በመጋፈጥ በድል ለመሻገር እያሳይ የነበረው ሚና ከፍተኛ እንደነበር ገልጸዋል።
የንግዱ ማህበረሰብ ኢኮኖሚያዊ ብልጽግና እንዲረጋገጥ የሚያደርገውን ተሳትፎ ይበልጥ በማጠናከር የልማት ጉዞዋችንን ማፋጠን ይጠበቅበታል ሲሉ ተናግረዋል።
በንግድ ስርዓቱ ፍትሐዊ የግብይት ስርዓትን ለመፍጠር መንግስት ችግሮችን ከነጋዴው ማህበረሰብ ጋር በጋራ እየፈታ ቀጣይነት እንዲኖረው ለማድረግ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።
የከተማው ማህበረሰብ ስራ ወዳድ፣ ሰላም ፈላጊ እና ከመንግስት ጎን በመሆን ልማትና ብልጽግና እንዲረጋገጥ አበክሮ የሚሰራ በመሆኑ ይህንን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አመላክተዋል።
በመድረኩ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ታደሰ ዋጄቦ፣ የጉራጌ ዞን ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አለማየሁ ገ/መስቀል፣ የዞኑ የሚመለከታቸው የመምሪያ ኃላፊዎች፣ የከተማው አመራሮች እና የንግዱ ማህበረሰብ ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ደጋጋ ኂሳቦ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
የኮንታ ዞን ም/ቤት 4ኛ ዙር 4ኛ ሥራ ዘመን 26ኛው መደበኛ ጉባኤው ተጠናቀቀ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ብሔረሰቦች ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ
አጫጭር የሙያ ክህሎት ስልጠና ማግኛታቸው በሚሰማሩበት የውጭ ሀገራት ሁሉ ተግባራቸውን እንዲወጡ እንደሚያስችላቸው በሆሳዕና ከተማ የሚገኙ ሰልጣኞች ተናገሩ