የወራቤ ዩንቨርሲቲ 3ኛ ዙር ሀገር አቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ እያካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ግንቦት 11/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የወራቤ ዩንቨረሲቲ ሶስተኛ ዙር ሀገር አቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ ከተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተውጣጡ ተመራማሪ ምሁራን እንዲሁም የክልል ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት እያካሔደ ነው፡፡
የጥናትና ምርምሩ ኮንፈረንስ “ጥናታዊ ምርምር ለዘላቂ እድገትና ማህበራዊ ለውጥ” በሚል መሪ ሀሳብ ነው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወራቤ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው፡፡
የዩንቨርስቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ኢንጂነር ቶፊክ ጀማል ባስተላለፉት መልዕክት የወራቤ ዩንቨረስቲ ከመማር ማስተማር ስራው በተጨማሪ ችግር ፈቺ የምርምር ስራዎች እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡
በምርምር ኮንፈረንሱ ላይ የተገኙት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፍቃዱ በትምህርት ስርዓቱ ውጤትን ለማሻሻል እና የትምህርት ስብራትን ለመጠገን መሥራት እንደሚጠበቅ ጠቁመው ማህረሰቡን ለመለወጥ የምርምር ስራ መስራት ይገባል ብለዋል፡፡
ዘጋቢ: ሳጂዳ ሙዳስር – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ