የወራቤ ዩንቨርሲቲ 3ኛ ዙር ሀገር አቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ እያካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ግንቦት 11/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የወራቤ ዩንቨረሲቲ ሶስተኛ ዙር ሀገር አቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ ከተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተውጣጡ ተመራማሪ ምሁራን እንዲሁም የክልል ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት እያካሔደ ነው፡፡
የጥናትና ምርምሩ ኮንፈረንስ “ጥናታዊ ምርምር ለዘላቂ እድገትና ማህበራዊ ለውጥ” በሚል መሪ ሀሳብ ነው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወራቤ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው፡፡
የዩንቨርስቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ኢንጂነር ቶፊክ ጀማል ባስተላለፉት መልዕክት የወራቤ ዩንቨረስቲ ከመማር ማስተማር ስራው በተጨማሪ ችግር ፈቺ የምርምር ስራዎች እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡
በምርምር ኮንፈረንሱ ላይ የተገኙት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፍቃዱ በትምህርት ስርዓቱ ውጤትን ለማሻሻል እና የትምህርት ስብራትን ለመጠገን መሥራት እንደሚጠበቅ ጠቁመው ማህረሰቡን ለመለወጥ የምርምር ስራ መስራት ይገባል ብለዋል፡፡
ዘጋቢ: ሳጂዳ ሙዳስር – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል