የወራቤ ዩንቨርሲቲ 3ኛ ዙር ሀገር አቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ እያካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ግንቦት 11/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የወራቤ ዩንቨረሲቲ ሶስተኛ ዙር ሀገር አቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ ከተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተውጣጡ ተመራማሪ ምሁራን እንዲሁም የክልል ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት እያካሔደ ነው፡፡
የጥናትና ምርምሩ ኮንፈረንስ “ጥናታዊ ምርምር ለዘላቂ እድገትና ማህበራዊ ለውጥ” በሚል መሪ ሀሳብ ነው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወራቤ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው፡፡
የዩንቨርስቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ኢንጂነር ቶፊክ ጀማል ባስተላለፉት መልዕክት የወራቤ ዩንቨረስቲ ከመማር ማስተማር ስራው በተጨማሪ ችግር ፈቺ የምርምር ስራዎች እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡
በምርምር ኮንፈረንሱ ላይ የተገኙት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፍቃዱ በትምህርት ስርዓቱ ውጤትን ለማሻሻል እና የትምህርት ስብራትን ለመጠገን መሥራት እንደሚጠበቅ ጠቁመው ማህረሰቡን ለመለወጥ የምርምር ስራ መስራት ይገባል ብለዋል፡፡
ዘጋቢ: ሳጂዳ ሙዳስር – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ