የክልሉ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ዋና ኦዲተር ወ/ሮ ፈዲላ አደም፤ የመስሪያ ቤቱ መቋቋም ዋና ዓላማ የሕዝብና የመንግስት ሀብትና ንብረት በትክክል ለታለመለት ዓላማ መዋሉን ማረጋገጥ እና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ ነው ብለዋል።
ለዚህም ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር መድረክ ፈጥሮ መወያየት ያለው ሚና የጎላ መሆኑን አመላክተዋል።
የክልሉ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት በአዋጅ 27/2016 በተሰጠው ስልጣንና ተግባር መሠረት እንዲሁም የተመርማሪዎች ግዴታ፣ የኦዲት አይነትና በኦዲት ወቅት በሚያጋጥሙ ችግሮች ዙሪያ በክልሉ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የኦዲት ጥራት ማረጋገጫ ዳይሬክተር በአቶ አበራ ጫኬቦ መወያያ ሰነድ ለውይይት ቀርቧል።
ካሉት 5 የኦዲት አይነቶች በክልሉ ተግባራዊ እየተደረጉ እንደሚገኙ የተመላከተ ሲሆን የመረጃ ስርዓት ወይም IT ኦዲት ብቻ ተግባራዊ መደረግ አለመጀመሩ ተገልጿል።
በመድረኩ የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባዔ ወ/ሮ መነቴ ሙንዲኖ፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት አቶ ኤርሲኖ አቡሬ፣ የክልሉ ዋና ኦዲተር ወ/ሮ ፈዲላ አደም፣ የክልል ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎችና አመራሮች፣ የሁሉም ዞንና ልዩ ወረዳዎች ዋና አፈ ጉባዔዎች፣ የከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንቶች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ አብደላ በድሩ

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ