የክልሉ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ዋና ኦዲተር ወ/ሮ ፈዲላ አደም፤ የመስሪያ ቤቱ መቋቋም ዋና ዓላማ የሕዝብና የመንግስት ሀብትና ንብረት በትክክል ለታለመለት ዓላማ መዋሉን ማረጋገጥ እና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ ነው ብለዋል።
ለዚህም ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር መድረክ ፈጥሮ መወያየት ያለው ሚና የጎላ መሆኑን አመላክተዋል።
የክልሉ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት በአዋጅ 27/2016 በተሰጠው ስልጣንና ተግባር መሠረት እንዲሁም የተመርማሪዎች ግዴታ፣ የኦዲት አይነትና በኦዲት ወቅት በሚያጋጥሙ ችግሮች ዙሪያ በክልሉ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የኦዲት ጥራት ማረጋገጫ ዳይሬክተር በአቶ አበራ ጫኬቦ መወያያ ሰነድ ለውይይት ቀርቧል።
ካሉት 5 የኦዲት አይነቶች በክልሉ ተግባራዊ እየተደረጉ እንደሚገኙ የተመላከተ ሲሆን የመረጃ ስርዓት ወይም IT ኦዲት ብቻ ተግባራዊ መደረግ አለመጀመሩ ተገልጿል።
በመድረኩ የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባዔ ወ/ሮ መነቴ ሙንዲኖ፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት አቶ ኤርሲኖ አቡሬ፣ የክልሉ ዋና ኦዲተር ወ/ሮ ፈዲላ አደም፣ የክልል ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎችና አመራሮች፣ የሁሉም ዞንና ልዩ ወረዳዎች ዋና አፈ ጉባዔዎች፣ የከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንቶች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ አብደላ በድሩ

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል