የክልሉ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ዋና ኦዲተር ወ/ሮ ፈዲላ አደም፤ የመስሪያ ቤቱ መቋቋም ዋና ዓላማ የሕዝብና የመንግስት ሀብትና ንብረት በትክክል ለታለመለት ዓላማ መዋሉን ማረጋገጥ እና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ ነው ብለዋል።
ለዚህም ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር መድረክ ፈጥሮ መወያየት ያለው ሚና የጎላ መሆኑን አመላክተዋል።
የክልሉ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት በአዋጅ 27/2016 በተሰጠው ስልጣንና ተግባር መሠረት እንዲሁም የተመርማሪዎች ግዴታ፣ የኦዲት አይነትና በኦዲት ወቅት በሚያጋጥሙ ችግሮች ዙሪያ በክልሉ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የኦዲት ጥራት ማረጋገጫ ዳይሬክተር በአቶ አበራ ጫኬቦ መወያያ ሰነድ ለውይይት ቀርቧል።
ካሉት 5 የኦዲት አይነቶች በክልሉ ተግባራዊ እየተደረጉ እንደሚገኙ የተመላከተ ሲሆን የመረጃ ስርዓት ወይም IT ኦዲት ብቻ ተግባራዊ መደረግ አለመጀመሩ ተገልጿል።
በመድረኩ የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባዔ ወ/ሮ መነቴ ሙንዲኖ፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት አቶ ኤርሲኖ አቡሬ፣ የክልሉ ዋና ኦዲተር ወ/ሮ ፈዲላ አደም፣ የክልል ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎችና አመራሮች፣ የሁሉም ዞንና ልዩ ወረዳዎች ዋና አፈ ጉባዔዎች፣ የከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንቶች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ አብደላ በድሩ

More Stories
የመሠረተ ልማት ችግሮችን ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ተገለጸ
በአከባቢዉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር እጥረት ችግር ለመቅረፍ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው
የአከባቢን እና የሀገርን ሰላም ለማረጋገጥ የሚቻለው ህብረተሰቡን የሰላም ባለቤት ማድረግ ሲቻል መሆኑ ተገለጸ