በጋብቻ፣ ፍቺና ንብረት ክፍፍል የህግ ማዕቀፎች እና አተገባበር ዙሪያ ከክልሉ ፍርድ ቤቶች ለተውጣጡ ዳኞች ስልጠና በአርባምንጭ ከተማ እየተሰጠ ይገኛል።
የክልሉን ህዝብ የፍትህ ጥማት ለማርካትና ተገቢውን አገልግሎት ለመስጠት በተለይም በፍትህ ተቋማት የሚታዩ የክህሎት፣ የስነ-ምግባርና የአሰራር ክፍተቶችን ለማረም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የፍትህና የህግ ኢንስቲትዩት በአዋጅ ቁጥር 13/2016 ተቋቁሞ ወደስራ ገብቷል።
በዚህም የፍትህ ስርዓቱን ዘመናዊ፣ ተደራሽ፣ ቀልጣፋና ውጤታማ ለማድረግ የሚረዱ የህግ ጥናትና ምርምሮችን እያካሄደ እንደሚገኝ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ካሳሁን ፍልፍሉ በእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግራቸው ገልፀዋል።
አክለውም “ፍትህ በገንዘብ ይሸጣል” የሚለው ወቀሳና ትችት የፍትህ ባለሙያዎች ሁሉም የክህሎት፣ የአመለካከት እና የስነ-ምግባር ችግር ስላለበት ሳይሆን እንደባለሙያዎቹ ባህሪ እና አቅም ሁኔታ የሚንፀባረቁ ችግሮች መሆናቸውን ገልፀው የሚታዩ ችግሮችን ታግለን በማረም የተቋማችንን ክብር መጠበቅ የሁላችንም ኃላፊነት ሊሆን ይገባል ብለዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንትና የፍትህ እና ህግ ኢንስቲትዩት ስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ቦጋለ ፈይሳ በመክፈቻ ንግግራቸው እንዳሉት፤ በጋብቻ፣ ፍቺና የንብረት ክፍፍል ዙሪያ ዳኞች በትኩረት መስራት አለባቸው።
ቤተሰብ የህብረተሰብ መሰረት፣ ህብረተሰብ ደግሞ የሀገር መሰረት መሆኑን ያወሱት አቶ ቦጋለ፤ ሀገርን ለመጠበቅ ሲባል ለቤተሰብ ህጉ ብርቱ ጥንቃቄ ማድረግ ከዳኝነት አካሉ እንደሚጠበቅ ገልጸው ስልጠናውን ወደ ተግባር መቀየር ይጠበቅብናል ሲሉ አሳስበዋል።
በጋብቻ፣ ፍቺና ንብረት ክፍፍል የህግ ማዕቀፎች እና አተገባበር ዙሪያ ከክልሉ ፍርድ ቤቶች ለተውጣጡ ዳኞች ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።
ዘጋቢ፡ ተመኙህ ገረሱ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል