የትምህርት ስብራትን ለመጠገን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው ተገለጸ
ሀዋሳ፡ ግንቦት 08/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) እንደሃገር እያጋጠመ ያለውን የትምህርት ስብራትን ለመጠገን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የድርሻውን ሊወጡ እንደሚገባ የወልቂጤ ዩንቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ፋሪስ ደሊል ገለጹ።
የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የስትራቴጂክ ጉዳይ ስራ አስፈጻሚዎች የምክክር መድረክ በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ነው።
የምክክር መድረኩ የተሻለ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነት በዩንቨርስቲዎች መረጋገጥን አላማ ያደረገ ስለመሆኑም ተገልጿል።
ዩንቨርስቲዎች የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ ኢትዮጵያን ወደ ከፍታ የሚያሻግር ትውልድ ማፍራት ላይ በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ ከመድረኩ ተመላክቷል።
የኢትዮጵያ የመንግስት ዩንቨርስቲዎች የምክክር መድረክ 47 አባል ዩንቨርስቲዎች ያሉት ሲሆን በዋናነት በትምህርት ጥራት ላይ በአመቱ የተከናወኑ ስራዎች ላይ ትኩረት የሚያደርግ ነው።
የዩንቨርስቲዎች የ2017 ዓ.ም እቅድ አፈፃፃም ሪፖርት የተዘጋጀ ግብረ መልስ እየቀረበ ይገኛል።
በመድረኩም የወልቂጤ ዩንቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ፋሪስ ደሊል፣ ከትምህርት ሚኒስቴር የተወከሉ እንግዶች እና ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እየተሳተፉ ይገኛል።
ዘጋቢ፡ አስቻለው አማረ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ