የትምህርት ስብራትን ለመጠገን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው ተገለጸ
ሀዋሳ፡ ግንቦት 08/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) እንደሃገር እያጋጠመ ያለውን የትምህርት ስብራትን ለመጠገን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የድርሻውን ሊወጡ እንደሚገባ የወልቂጤ ዩንቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ፋሪስ ደሊል ገለጹ።
የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የስትራቴጂክ ጉዳይ ስራ አስፈጻሚዎች የምክክር መድረክ በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ነው።
የምክክር መድረኩ የተሻለ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነት በዩንቨርስቲዎች መረጋገጥን አላማ ያደረገ ስለመሆኑም ተገልጿል።
ዩንቨርስቲዎች የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ ኢትዮጵያን ወደ ከፍታ የሚያሻግር ትውልድ ማፍራት ላይ በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ ከመድረኩ ተመላክቷል።
የኢትዮጵያ የመንግስት ዩንቨርስቲዎች የምክክር መድረክ 47 አባል ዩንቨርስቲዎች ያሉት ሲሆን በዋናነት በትምህርት ጥራት ላይ በአመቱ የተከናወኑ ስራዎች ላይ ትኩረት የሚያደርግ ነው።
የዩንቨርስቲዎች የ2017 ዓ.ም እቅድ አፈፃፃም ሪፖርት የተዘጋጀ ግብረ መልስ እየቀረበ ይገኛል።
በመድረኩም የወልቂጤ ዩንቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ፋሪስ ደሊል፣ ከትምህርት ሚኒስቴር የተወከሉ እንግዶች እና ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እየተሳተፉ ይገኛል።
ዘጋቢ፡ አስቻለው አማረ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ
ሁሉም ሰው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በቀጣይ የሚያስተዳድረውን መንግስት መምረጥ እንዲችል የምርጫ ካርድ በወቅቱ መያዝ እንደሚጠበቅበት ተገለጸ