የትምህርት ስብራትን ለመጠገን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው ተገለጸ
ሀዋሳ፡ ግንቦት 08/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) እንደሃገር እያጋጠመ ያለውን የትምህርት ስብራትን ለመጠገን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የድርሻውን ሊወጡ እንደሚገባ የወልቂጤ ዩንቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ፋሪስ ደሊል ገለጹ።
የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የስትራቴጂክ ጉዳይ ስራ አስፈጻሚዎች የምክክር መድረክ በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ነው።
የምክክር መድረኩ የተሻለ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነት በዩንቨርስቲዎች መረጋገጥን አላማ ያደረገ ስለመሆኑም ተገልጿል።
ዩንቨርስቲዎች የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ ኢትዮጵያን ወደ ከፍታ የሚያሻግር ትውልድ ማፍራት ላይ በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ ከመድረኩ ተመላክቷል።
የኢትዮጵያ የመንግስት ዩንቨርስቲዎች የምክክር መድረክ 47 አባል ዩንቨርስቲዎች ያሉት ሲሆን በዋናነት በትምህርት ጥራት ላይ በአመቱ የተከናወኑ ስራዎች ላይ ትኩረት የሚያደርግ ነው።
የዩንቨርስቲዎች የ2017 ዓ.ም እቅድ አፈፃፃም ሪፖርት የተዘጋጀ ግብረ መልስ እየቀረበ ይገኛል።
በመድረኩም የወልቂጤ ዩንቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ፋሪስ ደሊል፣ ከትምህርት ሚኒስቴር የተወከሉ እንግዶች እና ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እየተሳተፉ ይገኛል።
ዘጋቢ፡ አስቻለው አማረ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ