በትራፊክ አደጋ የ4 ሰዎች ሕይወት አለፈ
በወላይታ ሶዶ ከተማ ዛሬ ጠዋት በደረሰ የትራፊክ አደጋ የአራት ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡
አደጋው ከሃዋሳ ወደ ወላይታ ሶዶ ሲጓዝ የነበረ በተለምዶ ዶልፊን ተብሎ የሚጠራ አነስተኛ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ በተቃራኒ አቅጣጫ ሲጓዝ ከነበረ ከባድ የጭነት ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ ነው የተከሰተው፡፡
በተከሰተው አደጋም የአራት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የወላይታ ሶዶ ከተማ ፖሊስ የትራፊክ አደጋ መከላከልና መቆጣጠር ዘርፍ አስተዳደር ዋና ሳጅን ዝናቡ ገዛኸኝ ተናግረዋል።
በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች አቅራቢያቸው በሚገኙ ጤና ተቋማት ሕክምና እየተከታተሉ መሆኑን ዋና ሳጅን ዝናቡ ገልጸዋል፡፡
ዘጋቢ፡ በቀለች ጌቾ – ከዋካ ቅርንጫፍ
More Stories
በክልሉ ከተለያዩ መገናኛ ብዙኃን የተውጣጡ የሚዲያ ባለሙያዎች ቡድን በሚዛን አማን ከተማ አረንጓዴ አሻራ አሳረፉ
የሲዳማ ክልላዊ መንግሥት 5ኛ አመት የምስረታ በዓል በተለያዩ ስነ ስርዓቶች እየተከበረ ነው
በክልሉ በተያዘው የበልግ ወቅት በኩታገጠም ሩዝና በቆሎ እያለሙ ያሉ አርሶአደሮች ተስፋ ሰጪ የሆነ የምርት ውጤት እንድናይ አስችሎናል አሉ።