በትራፊክ አደጋ የ4 ሰዎች ሕይወት አለፈ
በወላይታ ሶዶ ከተማ ዛሬ ጠዋት በደረሰ የትራፊክ አደጋ የአራት ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡
አደጋው ከሃዋሳ ወደ ወላይታ ሶዶ ሲጓዝ የነበረ በተለምዶ ዶልፊን ተብሎ የሚጠራ አነስተኛ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ በተቃራኒ አቅጣጫ ሲጓዝ ከነበረ ከባድ የጭነት ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ ነው የተከሰተው፡፡
በተከሰተው አደጋም የአራት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የወላይታ ሶዶ ከተማ ፖሊስ የትራፊክ አደጋ መከላከልና መቆጣጠር ዘርፍ አስተዳደር ዋና ሳጅን ዝናቡ ገዛኸኝ ተናግረዋል።
በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች አቅራቢያቸው በሚገኙ ጤና ተቋማት ሕክምና እየተከታተሉ መሆኑን ዋና ሳጅን ዝናቡ ገልጸዋል፡፡
ዘጋቢ፡ በቀለች ጌቾ – ከዋካ ቅርንጫፍ
More Stories
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሪጅን በሚዛን ዲስትሪክት አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ለማረጋገጥ ቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ
የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በዘላቂነት ለመፍታት በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ
በኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች የህግ ትምህርት ቤቶች መካከል የተካሄደው 9ኛው የምስለ ችሎት ውድድር በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ አሸናፊነት ተጠናቀቀ