የዞኑ ሕዝብ ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ ወ/ሮ ሀብታምነሽ ግራዝማች ባደረጉት የመግቢያ ንግግር፤ ምክር ቤቶች በሕገ-መንግስት የተሰጣቸውን ሥልጣን ተግባር እየፈፀሙ የዞኑ ሕዝብ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ጉዞ እንዲፈጥን እንዲሁም የሕዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሆናቸውን አብራርተዋል።
የምክር ቤቱ አባላት ያለፈውን 6ኛ አስቸኳይ ረቂቅ ቃለ ጉባኤ መርምረው አጽድቀዋል።
የምክር ቤቱ የ9 ወራት የሥራ ሪፖርት በዝርዝር ለአባላቱ የቀረበ ሲሆን የዞን፣የወረዳ፣የከተማና የቀበሌያት ምክር ቤቶች የመደበኛ ጉባኤ አፈጻጸም ያለበት ደረጃ በጠንካራ ጎን ተገምግሟል።
የቋሚ ኮሚቴዎች ድጋፍና ክትትል በተመሣሣይ በጠንካራ ጎን ቢገለፅም በዞኑ በተለያዩ ዘርፎች የሚገኘውን አጠቃላይ የጥሬ ገንዘብ ዕዳ ከማስመለስ ረገድ ሰፊ ስራ የሚጠበቅበት መሆኑ ተመላክቷል።
ከኦዲት ግኝት ከማስመለስ አንጻር የታየው ደካማ አፈጻጸም በአስቸካይ ሊታረም እንደሚገባው በምክር ቤቱ አባላት አስተያየት ተሰጥቶበታል።
የጎፋ ዞን አስተዳደር ምክር ቤት የ9 ወራት ሪፖርት በዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ ቀርቧል፡፡
ምክር ቤት ለሁለት ተከታታይ ቀናት በሚኖረው ቆይታ ልዩ ልዩ ሹመቶችን ምርምሮ እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል፡፡
ዘጋቢ: አወል ከድር – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
በመንግስት ድጋፍና በህብረተሰቡ ተሣትፎ የተገነባው ጤና ጣቢያ በጎፋ ዞን ደንባ ጎፋ ወረዳ ወይዴ ውርኪ ማዕከል ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
የሳውላ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ወንጀልን የሚጸየፉ አምራች ዜጎችን ለማፍራት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገለፀ
በዳውሮ ዞን ገና ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የምረጡኝ ቅስቀሳና የፓርቲ ምርጫ ምልክት የማስተዋወቅ መርሃ ግብር ተካሄደ