የዞኑ ሕዝብ ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ ወ/ሮ ሀብታምነሽ ግራዝማች ባደረጉት የመግቢያ ንግግር፤ ምክር ቤቶች በሕገ-መንግስት የተሰጣቸውን ሥልጣን ተግባር እየፈፀሙ የዞኑ ሕዝብ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ጉዞ እንዲፈጥን እንዲሁም የሕዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሆናቸውን አብራርተዋል።
የምክር ቤቱ አባላት ያለፈውን 6ኛ አስቸኳይ ረቂቅ ቃለ ጉባኤ መርምረው አጽድቀዋል።
የምክር ቤቱ የ9 ወራት የሥራ ሪፖርት በዝርዝር ለአባላቱ የቀረበ ሲሆን የዞን፣የወረዳ፣የከተማና የቀበሌያት ምክር ቤቶች የመደበኛ ጉባኤ አፈጻጸም ያለበት ደረጃ በጠንካራ ጎን ተገምግሟል።
የቋሚ ኮሚቴዎች ድጋፍና ክትትል በተመሣሣይ በጠንካራ ጎን ቢገለፅም በዞኑ በተለያዩ ዘርፎች የሚገኘውን አጠቃላይ የጥሬ ገንዘብ ዕዳ ከማስመለስ ረገድ ሰፊ ስራ የሚጠበቅበት መሆኑ ተመላክቷል።
ከኦዲት ግኝት ከማስመለስ አንጻር የታየው ደካማ አፈጻጸም በአስቸካይ ሊታረም እንደሚገባው በምክር ቤቱ አባላት አስተያየት ተሰጥቶበታል።
የጎፋ ዞን አስተዳደር ምክር ቤት የ9 ወራት ሪፖርት በዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ ቀርቧል፡፡
ምክር ቤት ለሁለት ተከታታይ ቀናት በሚኖረው ቆይታ ልዩ ልዩ ሹመቶችን ምርምሮ እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል፡፡
ዘጋቢ: አወል ከድር – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
የመድሀኒት ተቋማት ስታንዳርድ ትግበራ የዳሰሳ ጥናት ውጤት ይፋ ማድረጊያ መርሀግብር ተካሄደ
በዶሮ እርባታ ዘርፍ በመሰማራት የተሻለ ውጤት እያስመዘገቡ መሆናቸውን የየም ዞን ሣጃ ከተማ በዘርፉ የተሰማሩ ሰዎች ተናገሩ
የከተማውን መሰረተ ልማት ከማሟላት ባሻገር ለነዋሪዎች ምቹ እና ማራኪ በማድረግ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ