የዞኑ ሕዝብ ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ ወ/ሮ ሀብታምነሽ ግራዝማች ባደረጉት የመግቢያ ንግግር፤ ምክር ቤቶች በሕገ-መንግስት የተሰጣቸውን ሥልጣን ተግባር እየፈፀሙ የዞኑ ሕዝብ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ጉዞ እንዲፈጥን እንዲሁም የሕዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሆናቸውን አብራርተዋል።
የምክር ቤቱ አባላት ያለፈውን 6ኛ አስቸኳይ ረቂቅ ቃለ ጉባኤ መርምረው አጽድቀዋል።
የምክር ቤቱ የ9 ወራት የሥራ ሪፖርት በዝርዝር ለአባላቱ የቀረበ ሲሆን የዞን፣የወረዳ፣የከተማና የቀበሌያት ምክር ቤቶች የመደበኛ ጉባኤ አፈጻጸም ያለበት ደረጃ በጠንካራ ጎን ተገምግሟል።
የቋሚ ኮሚቴዎች ድጋፍና ክትትል በተመሣሣይ በጠንካራ ጎን ቢገለፅም በዞኑ በተለያዩ ዘርፎች የሚገኘውን አጠቃላይ የጥሬ ገንዘብ ዕዳ ከማስመለስ ረገድ ሰፊ ስራ የሚጠበቅበት መሆኑ ተመላክቷል።
ከኦዲት ግኝት ከማስመለስ አንጻር የታየው ደካማ አፈጻጸም በአስቸካይ ሊታረም እንደሚገባው በምክር ቤቱ አባላት አስተያየት ተሰጥቶበታል።
የጎፋ ዞን አስተዳደር ምክር ቤት የ9 ወራት ሪፖርት በዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ ቀርቧል፡፡
ምክር ቤት ለሁለት ተከታታይ ቀናት በሚኖረው ቆይታ ልዩ ልዩ ሹመቶችን ምርምሮ እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል፡፡
ዘጋቢ: አወል ከድር – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በጋሞ ዞን በተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ከ5 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ
የወረዳውን ዕድገት ለማፋጠን የተጀመሩ የመሰረተ ልማት ተቋማት ሊፋጠኑ ይገባል
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደና የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በወ/ሮ አዱኛ አዛዥ ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ሀዘን ገለጹ